Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Saturday
Oct 11th
Home arrow Sections arrow የልደት ቅኔ - ዘአምላኪየ
የልደት ቅኔ - ዘአምላኪየ E-mail
Tuesday, 08 January 2008
ልደተ ክርስቶስ ባዕል አወፈዮሙ በቃና፣
ሀሊበ ለሙሴ ወለጴጥሮስ መና፣
እስመ ይገብር ምሕረት በዘቦ ክሂሎተ ኲሉ ብዕልና፡፡

ትርጉም

የክርስቶስ ልደት/ባለጠጋ፣
ለሙሴ ወተትን፣ ለጴጥሮስም ዳቦን በቃና ሰጣቸው፣
ባለው ሁሉን መቻል/ ብልጥግና ርህራሄን ያደርጋልና፡፡

ምስጢር

ሃብታም ሰው ለአንዱ ወተት ለሌላውም ዳቦ እንደፍላጎቱ ሊሰጥ እንደሚችል፣ የክርስቶስ ልደት ለሙሴ ወተት ለጴጥሮስም ዳቦ ሰጣቸው፤ ማለት ውሃውን ወተት ድንጋዩንም ዳቦ አደረገ ማለት እንደሆነ በቅኔው ተመስጥሮአል፡፡

ታሪክ

ሙሴ ማለት በጥንት የግብፃውያን ቋንቋ ውሃ ወይም ከውሃ የተገኘ ማለት ነው /ዘፀአ. 2፡10/፡፡ ጴጥሮስ ማለትም በግሪክ ቋንቋ ድንጋይ ማለት ነው /ማቴ. 16፡18/፡፡ ክርስቶስ በተወለደበት እለት የወንዞች ውሃ ወተት፣ ወይንና መአር፣ ድንጋዮችም ዳቦ ሆነዋል፡፡ እንጨቶችም ሁሉ ጣፋጭ ፍሬ አፍርተዋል ይባላል /ዝማሬ ዘልደት/፡፡

/የግእዝ ቅኔያት የስነ ጥበብ ቅርስ 3ኛ፣ 1995/

 

 
< Prev   Next >