| አገራዊ የዋጋ ግሽበት 18 በመቶ ደረሰ |
|
|
| Wednesday, 19 March 2008 | |
|
የአገሪቱ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት በየካቲት 2000 ዓ.ም 18 በመቶ መድረሱን የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ያወጣው የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክስ አመለከተ፡፡
በኢንዴክሱ መሠረት በየካቲት ወር 2000 ዓ.ም የተመዘገበው አገራዊ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 18 በመቶ ሲሆን ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ከታየው 13.5 በመቶ የዋጋ ግሽበት ጋር ሲነፃፀር በ4.5 ጭማሪ አሳይቷል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በየካቲት ወር 2000 ዓ.ም የተመዘገበው አገራዊ የምግብ ዋጋ ግሽበት 23.7 በመቶ መሆኑ ታውቋል፡፡ በየካቲት ወር 10.5 በመቶ አገራዊ ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት ተከስቷል፡፡ ኢንዴክሱ በየካቲት ወር 2000 ዓ.ም የተመዘገበው 23.7 በመቶ የምግብ የዋጋ ግሽበት ከየካቲት 1999 በጀት አመት ከታየው 14.5 ጋር ሲነፃፀር 9.2 ጭማሪ ማሳየቱን አመላክቷል፡፡ ለምግብ ዋጋ ግሽበት በበርበሬ ዋጋ ላይ የታየው የዋጋ ንረት በዋነኝነት ተጠቃሽ ሆኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የየካቲት ወር 2000 ዓ.ም የአገር አቀፍ ጠቅላላ የችርቻሮ ዋጋ ኢንዴክስ ከየካቲት ወር 1999 ዓ.ም ጠቅላላ ኢንዴክስ ጋር ሲነፃፀር 22.9 ከመቶ ማደጉ ታውቋል፡፡ በተሾመ ንቁ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |