| አል አሙዲን በደቡብ አፍሪካ... |
|
|
| Wednesday, 19 March 2008 | |
![]() ሼህ መሐመድ አል አላሙዲን ሼህ መሐመድ አል አላሙዲን በደቡብ አፍሪካ ዋና ከተማ ጆሃንስበርግ ውስጥ ሳንድቶን በተባለ አካባቢ የሚገኝን መኖሪያና ሆቴል ያረፈበትን መሬት ለመግዛት በሂደት ላይ መሆናቸውን ዘ ታይምስ የተባለው የደቡብ አፍሪካ ጋዜጣ ይፋ አደረገ፡፡ ከትናንት በስቲያ በተሰራጨው ይኸው ጋዜጣ ዘገባ መሠረት ከአለማችን ቱጃሮች አንዱ የሆኑት ሼህ መሀመድ አልአሙዲ ከአለማችን ቱጃሮች መካከል በ97ኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ መሆናቸውን ጠቅሶ በሰሜናዊ ጆሃንስበርግ ሳንድቶን በተባለ አካባቢ የሚገኘው ይህ ቦታ 11ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት እንዳለው አመልክቷል፡፡ የመሬቱ እና የንብረቱ ዋጋ 200 ሚሊዮን የደቡብ አፍሪካ ራንድ የተገመተው ይህ ቦታ ጆሃንስበርግ ውስጥ ከሚገኙ አንደኛ ደረጃ ከሚሰጣቸው ቦታዎች አንዱና ሐብታሞች የሚኖሩበት አካባቢ ነው፡፡ አላሙዲን ይህን ሊገዙት ያሰቡትን ቦታ በግንባር ተገኝተው መመልከታቸውን ጋዜጣው ጠቁሟል፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ የመሬቱ ባለቤቶች አስተያየት ለመስጠት ፍቃደኛ ባይሆኑም አልአሙዲን መሬቱን ለመግዛት ፍላጎት ካሳዩ ወገኖች የሚመደቡ ሲሆን እስከ 150 ሚሊዮን ራንድ ለማውጣት ተስማምተዋል፡፡ በመሬቱ ላይ 35 ልዩ ልዩ የመኖሪያ ቤቶችና 125 ክፍሎች ያሉት ሆቴል ያለው ሲሆን ባለሃብቱ በቦታው ላይ ምን አይነት ግንባታ እንደሚያካሂዱበት ግን አልጠቀሰም፡፡ በጋዜጣው ዜና መሠረት፣ የአልአሙዲን የግዢ ሃሳብ ከተሳካ በደቡብ አፍሪካ ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የውጪ አገር ቢሊየነሮች አንዱ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ ባለፈው ዓመት ይህንን ቦታ ለመግዛት 138 ሚሊዮን ራንድ ቀርቦ እንደነበር ጋዜጣው አስታውሷል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |