| የሁለት ሲሚንቶ ፋብሪካዎች... |
|
|
| Wednesday, 19 March 2008 | |
|
የሁለት ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ምርት የጥራት ደረጃ እየተፈተሸ ነው
የማምረት ሥራ የጀመሩ ሁለት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የሚያመርቱትን ሲሚንቶ የጥራት ደረጃን የኢትዮጵያ ጥራትና ደረጃ ባለሥልጣን እየፈተሸመሆኑ ተገለፀ፡፡ የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሲሳይ አሰፌ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት፣ ባቀረቡት ናሙና መሠረት ፍተሻ እየተደረገባቸው ያሉት ሲጂሲ እና አቢሲኒያ የተባሉ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ናቸው፡፡ በቻይናና በሕንድ ባለሃብቶች የተቋቋሙት ሁለቱ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የማምረት ሥራ የጀመሩ ሲሆን ምርታቸውን በቀጥታ ለገበያ ከማቅረባቸው በፊት በባለሥልጣኑ የምርታቸውን ጥራት ማረጋገጫ ማግኘት እንደሚገባቸው የጠቆሙት አቶ ሲሳይ ከማረጋገጫው በፊት ምርታቸውን ለገበያ ከማቅረብ ይልቅ ማረጋገጫ ካገኙ በኋላ መሸጡ ተመራጭ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሁለቱም ፋብሪካዎች ምርት ናሙናዎች በባለሥልጣኑ ባለሙያዎች እየተፈተሹ ቢሆንም ደረጃቸውን ጠብቀዋል አልጠበቁም የሚለውን ውጤት ለመግለፅ 25 ቀናት አካባቢ ይወስዳል፡፡ ከፋብሪካዎቹ ናሙና የተወሰደው ከአንድ ሳምንት በፊት እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ በሌላ በኩል ግን ሲጂሲ የተባለው የቻይና ኩባንያ በቆቃ አካባቢ በተከለው ፋብሪካው በማምረት ላይ የሚገኘውን ሲሚንቶ ለገበያ ማቅረቡን ይፋ አድርጓል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |