Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
May 09th
Home
Headline
  • Pause
  • Previous
  • Next
1/10
Image 'ከኤርትራ ጋር ጦርነት ሊፈነዳ ይችላል' ጅቡቲ
በጋዜጣው ሪፖርተር

የኤርትራና የጅቡቲ ወታደሮች መፋጠጣቸውንና ጦርነት ሊፈነዳ የሚችል መሆኑን የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ማስታወቃቸውን ሮይተር የዜና ወኪል ዘገበ፡፡

Read more...
 
Zena
Image የኤርትራ ተቃዋሚዎች በጀመሩት ጉባኤ...
የኤርትራ ተቃዋሚዎች በጀመሩት ጉባኤ የስደት መንግሥት ለማቋቋም አስበዋል

በየማነ ናግሽ

በኤርትራው ኘሬዚዳንት አሳያስ አፈወርቂ ስርዓት ተማረው ትግል የጀመሩ 13 ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ አንድነታቸውን አጠናክረውና በአንድ ጥላ ስር ሆነው ለመታገል በአዲስ አበባ የአንድነት ጉባኤ ጀመሩ፡፡ የስደት መንግሥት ለማቋቋም ፍላጎት አላቸው፡፡

Editorial
Image ከሕንፃና የመንገድ ግንባታ ጎን ለጎን...
ከሕንፃና የመንገድ ግንባታ ጎን ለጎን የፍትሕና የመልካም መስተዳድር ግንባታ ይኑር!

አዲስ አበባ እንደገና እየተሰራች ነው፡፡ አሌ የማይባል ግልፅና ገሃድ ሃቅ ነው፡፡ በርካታ ትላልቅ መንገዶችና ድልድዮች እየተገነቡ ነው፡፡ በርካታ አዳዲስ ሕንፃዎች ተሰርተዋል፣ እየተሰሩም ናቸው፡፡ በዚህም አዲስ አበባ ከአፍሪካ ትላልቅ ከተሞች እንዷ ልትሆን ትችላለች፡፡ አዲስ አበባን እንደገና ሠራኋት ብሎ ኢሕአዴግ ቢኮራ አያሳፍረውም፡፡

 
Politics
የዜግነት ስሜት
በሰለሞን ጎሹ

ከበርካታ ጥናቶችም ሆነ ከተግባራዊ ልምዳችን አንፃር የኢትዮጵያ ተወላጆች ወደ ውጭ በተለይም ወደ ምዕራብ አውሮፓና አሜሪካ ለማቅናት ሕልም ያላቸውና አጋጣሚን የሚጠቀሙ በርካቶች ናቸው፡፡ ለአንዳንዶች የኑሮ ማሻሻያና የተሻለ ሥራ ፍለጋ ይሁን እንጂ ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉት ግን የዜግነት ስሜታቸው በጣም ቀዝቃዛ በመሆኑና ከሌሎች ጠንካራ የዜግነት ስሜት ካላቸው ቡድኖች ጋር መመሳሰል ስላልቻሉ ሀገር የሚለቁ እንደሆኑ የአንዳንድ ጥናቶች መረጃ ያመለክታል፡፡

Briefs
በድሬዳዋ አንድ ተሽከርካሪ...
በድሬዳዋ አንድ ተሽከርካሪ በውሃ ተወስዶ ሁለት ሰዎች ሞቱ

ጀልዴሳ ከተባለ የገጠር ቀበሌ አምስት ስዎች አሳፍሮ ወደ ድሬዳዋ ይጓዝ የነበረ ቶዮታ ላንድ ክሩዘር መኪና ከትናንት በስቲያ በደራሽ ውሃ ሙላት በመውሰዱ በውስጡ ከነበሩት መካከል ሁለቱ ሲሞቱ አንድ ሰው በጽኑ መቁሰሉን የድሬዳዋ ጊዜያዊ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

 
Business & Economy
በነጋዴዎች በሸማቾችና በመንግሥት...
በነጋዴዎች በሸማቾችና በመንግሥት መካከል የጋራ መግባባት እንዲፈጠር ተጠየቀ

በቤዛዊት ሥዩም

የኢትዮጵያ የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ሕዝባዊ የምክክር መድረክ ባለፈው ሐሙስ ሚያዚያ 23 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም. በሂልተን ሆቴል በኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበትና የኑሮ ውድነት ዘላቂ የመፍትሄ ሃሳቦች በሚል ባካሄደው ውይይት ላይ እንደተገለፀው የኑሮ ውድነት በህብረተሰቡ ላይ እየፈጠረ ያለውን ጫና ለመቀነስ በነጋዴዎች፣ በሸማቾችና በመንግሥት መካከል የጋራ መግባባት መፍጠር ያስፈልጋል፡፡

Shemach
የደብረ ብርሃን አገልግሎት ሰጪዎች
ሊያ አዳነ

ጥራት ስንል የተለያዩ መመዘኛዎች ልናወጣለት እንችላለን፡፡ በገበያ ውስጥ የሚፈጠር የንግድ ውድድር ይህን ጥራት ለማስገኘት ያስችላል፡፡ የአልግሎት ሰጪዎች፣ አምራቾችና ነጋዴዎች ያላቸውን የሽያጭ ድርሻ ለማሳደግ የተለያዩ ስልቶችን ይከተላሉ፡፡
 
Interview
Image "በአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ የእስከዛሬ...
"በአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ የእስከዛሬ መዳከም ሁላችንም ተጠያቂዎች ነን"
አቶ ሚሊዮን በላይ፣ የመልካ ማኅበር ዋና ዳይሬክተር

አቶ ሚሊዮን በላይ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ የተማሩት በአዲስ አበባ ነው፡፡ በባዮሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከእንግሊዝ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኬንት በቱሪዝም ኤንድ ኮንሰርቬሽን ተቀብለዋል፡፡

Fermata
ጤና
በኢትዮጵያ ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎት ለመጀመሪያ ጊዜ መስጠት የተጀመረው በአፄ ልብነ ድንግል ዘመን ከፖርቱጊዝ የዲፕሎማቲክ ሚሲዮን ጋር አብሮ በመጣውና ንጉሡን ከ1512-1527 ሲያገለግል በቆየ ሐኪም አማካኝነት ነበር፡፡ እስከ አፄ ምኒሊክ ዘመነ መንግሥት ድረስ በተለያዩ ጊዜያት በተመሳሳይ ሁኔታ የውጭ ሀገር ሐኪሞች እየመጡ ነገሥታቱን ሲያገለግሉ እንደነበር የተገኙት የጽሑፍ መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡

 
Kibur Minister
ክቡር ሚኒስትር
(የታዳጊ አገሮች ኢኮኖሚን ማዳበር በሚመለከት በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ለመሳተፍ ክቡር ሚኒስትሩ ወደ ጄኔቭ እየተጓዙ ናቸው፡፡ አገራቸው ውስጥ ኢንቨስት ለማድረግ የመጡት ኢትዮጵያዊው ዲያስፖራም ከጀርመን ማሽነሪ ለመግዛት እየተጓዙ ናቸው፡፡ እንዳጋጣሚ አውሮፕላን ውስጥ አብረው ተቀምጠዋል)
Life & Art
Image ኦርኬስትራ ኢትዮጵያ እንደገና
በሔኖክ ያሬድ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ራስ መኮንን አዳራሽ ዓርብ ሚያዚያ 24 ቀን 2000 ዓ.ም አንድ ትዕይንት ቀረበ፡፡ በባህል ዙሪያ ያጠነጠነ ነው፡፡ ከአራት ዐሥርት ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ የኖረ የኦርኬስትራ ኢትዮጵያ አስተባባሪ አሜሪካዊ ቻርልስ ሳተን በኢትዮጵያ ባህላዊ ልብስ እጀ ጠባብ ደምቆ ይታያል፡፡
 
Social
Image ለ3ዐ ዓመታት
ጐመን ከመሸጥ ፈቀቅ ያላለ ኑሮ

በምሕረት አስቻለው

ልደታ ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት አስፋልት ዳር ላይ ጐመንና ቆስጣ የሚሸጡ በርካታ ሴቶች አሉ፡፡  ከሌሎቹ ገንጠል ብለው የተመለከትናቸውን በእድሜ የገፉ እናት ቀርበን አነጋገርናቸው፡፡ ወ/ሮ አስናቀች በለው ይባላሉ፡፡ እድሜአቸው በግምት በስልሳዎቹ አጋማሽ ላይ ይሆናል፡፡ የአምስት ልጆች እናት ሲሆኑ ባለቤታቸው በመሞታቸው ልጆቻቸውን ለብቻቸው ማሳደጋቸውን ገልፀውልናል፡፡
Science & Technology
የሚጥል በሽታን በምግብ መከላከል ይቻላል
ሕፃናት ላይ የሚከሰትን የሚጥል በሽታ የተለየና ከፍተኛ የቅባትነት ይዘት ያለው ምግብ በመመገብ መቀነስ እንደሚቻል የእንግሊዝ ተመራማሪዎች አስታወቁ፡፡

 
Diaspora
የአውሮፓ ህብረት ፖሊሲ...
የአውሮፓ ህብረት ፖሊሲ አውጪዎችና የአፍሪካ ዲያስፖራዎች ይወያያሉ

በጋዜጣው ሪፖርተር

ዲያስፖራው ስደትን ለማርገብም ሆነ በልማት ለመሳተፍ ቁልፍ ሚና ስላለው የአውሮፖ ፖሊሲ አውጪዎች በመጪው ሰኔ ወር ከአፍሪካዊያኑ ዲያስፖራ ጋር በብራስልስ ለውይይት ይቀመጣሉ፡፡
Youth
Image ወጣቱ ዲን
በምሕረት አስቻለው

ምስጋናው ሙሉጌታ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት ዲን ነው፡፡ የሕግ ትምህርቱን በ1999 ዓ.ም በጅማ ዩኒቨርሲቲ አጠናቋል፡፡ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መሥራት ከጀመረ ስምንት ወር ሆኖታል፡፡ የዛሬ ስምንት ወር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሲቀጠር አብዛኞቹ መምህራን ልክ እንደሱ ትምህርታቸውን አጠናቅቀው መምህራን ለመሆን የተመደቡ ነበሩ፡፡ ስለነበሩና ዩኒቨርሲቲውም አዲስ ስለነበር በቢዝነስ ፋኩልቲ ሥር ለተቋቋመው ሕግ ዲፓርትመንት አስተባባሪ ሆኖ መመረጡን ነግሮናል፡፡
 
Opinion
የ"ጥሩ እና በቂ" የፕሬስ ሕግ...
የ"ጥሩ እና በቂ" የፕሬስ ሕግ ረቂቅ ግብና ዓላማ ምንድነው?

(አስፋው ነጻነት)

ሕግ አውጪው አንድን ሕግ የሚያወጣው፤ የሚያፀድቀው አንድ ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ዓላማዎች ይዞና ጨብጦ ነው፡፡ ሊደርስባቸው በሚፈልጋቸው ዓላማዎችና ግቦች ላይ ከወዲሁ አነጣጥሮ፣ አልሞ፣ ለአተረጓጐማቸው ወጥነት ለተፈጻሚነታቸው እርግጥኛነት ተጠቦና ተጨንቆ መሆን አለበት፡፡
Letter to Reporter
ሕዝቡ የልማት ጥሙን ካረኩለት ይተባበራል
አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የአፍሪካ መዲና ናት፡፡ የበርካታ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መናኸሪያ ናት፡፡ ይሁን እንጂ በልማትና በተወሳሰቡ ችግሮች የተዘፈቀች ናት፡፡ ከመሬት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ሙስና የሚፈጸምባት ሆናለች፡፡ ድህነት በጣም ተንሰራፍቶባታል፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ የምትገኘውን አዲስ አበባን በከንቲባነት ለማስተዳደር ብልህነትን፣ አርቆ አስተዋይነትን፣ ቆራጥነትን፣ ከሙስና መጽዳትን፣ ብቃት ያለው አመራር ሰጪነትን ያስፈልጋል፡፡ ከተማን የማስተዳደር ልምድ ያካበተ ሰው ሊሆን ይገባል፡፡  

 
Women
ልጅም ሚስትም?
በትዕግሥት ዘሪሁን

የቤተሰቡ ስድስተኛና ብቸኛ ሴት ልጅ ናት፡፡ ከልጅነቷ ጀምሮ በእናቷና አባቷ መካከል ስምምነት እንደሌለ ትናገራለች፡፡ የጭቅጭቅ ኑሯቸው የተለመደ ቢሆንም አንድ ቀን ግን እናታቸው ቤቱን ጥላ እንደወጣች ታስታውሳለች፡፡ ከዚያ በኋላ ኑሯቸው ተቀየረ፡፡ አባት ከድሮው በባሰ እየሰከረ ይገባል፡፡ እቤቱ ውስጥ ያለው ኃላፊነት በብዛት በወቅቱ 15 ዓመት ባልሞላት ይህችው ታዳጊ ትከሻ ላይ ወደቀ፡፡ ተመላላሽ ሠራተኛ ቀጥረው የሚያሰሩ ቢሆንም የሚያስፈልጉ ነገሮችን መገዛዛትና እናቷን ተክታ ቤቱን መቆጣጠር ነበረባት፡፡ ሥራ መሥራት ግን አትችልም፡፡ "ቤት መጥረግ እንኳን የለመድኩት ስምንተኛ ክፍል ስደርስ ነው" ትላለች፡፡
Temuaget
ለብሔራዊ ባንክ በሽታ...
ለብሔራዊ ባንክ በሽታ መፍትሄው
ፓራሲታሞል ወይስ ቀዶ - ጥገና?

በአባዋሪ ጅብሪል

አንድ በሽተኛ ወደ ሆስፒታል ሲሄድ ዶክተሩ ከመረመረው በኋላ እንደ በሽታው አይነትና ክብደት መድሀኒት ያዝለታል፡፡ በዚሁ መሰረት እስካሁን የተገለጹትንና ያልተገለጹትን የብሔራዊ የባንክ መጠነ ሰፊ ችግሮች ስናጤናቸውና በአሁኑ ሰአት የገባበትን አዘቅት ስንመለከት በእርግጥ ለባንኩ በሽታ የሚያስፈልገው ለማስታገሻ የሚሆን ፓራሲታሞል ወይስ አጠቃላይ ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል ሥር-ነቀል ለውጥ"ቀዶ ጥገና"? የሚል ጥያቄ እንድናነሳ አድርጎናል፡፡
 
Law
የዋስትና መብት እንዴት ይከለከላል?
በሰለሞን ጎሹ

ከዚህ ቀደም በዚህ አምድ ላይ ስለዋስትና አንዳንድ ጠቃሚ ነጥቦችን ከ"የዳኞች መርሀ ችሎት" ላይ በመውሰድ ማውጣታችን አይዘነጋም፡፡ ይሁንና ከታዋቂው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ክስና ዋስትና መከልከል በመነሳት በርካታ የሕግ ባለሙያዎች በኢትዮጵያ የዋስትና ሕግ ላይ ክርክር የሚያደርጉበት አጋጣሚ ተፈጥሯል፡፡ የወንጀለኛ መቅጫ ስነ ስርዓት ሕጉን ለማሻሻል መንግሥት እየተንቀሳቀሰ በመሆኑ በጉዳዩ ላይ የሚሰጡ ትንታኔዎች የራሳቸውን አስተዋፅኦ ማበርከታቸው አይቀርም፡፡
Zennk
የአስተሳሰብ ድምር
ያልበሰሉ ሰዎች ፣ዕድል፣ ወይም ፣ዕጣ፣ በሚባል ጣጣ ያሳብባሉ፡፡ ግባቸውን የሚያሰምርላቸው መለኮት በውስጣቸው ያለ መሆኑን የሚያስገነዝባቸው ኮርኳሪ ይፈልጋሉ፡፡ አስተሳሰብና ስብዕና የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው፡፡ በለም አፈር በሚመሰለው የአእምሯችን ጓዳ የምንኮተኩተው ዘር ለማንኛውም አቅጣጫ፣ ለድል ይሁን ለሽንፈት መሠረት መሆኑን መገንዘብ አለብን፡፡
 
Delalaw
ወርውር - የድርሻህን
የተለያዩ ማመልከቻዎችን እናረቅቃለን፡፡ ቢጋር እንነድፋለን፡፡ ከእነዚህ መካከል የጽሑፍና የአእምሮ ይገኙበታል፡፡ ጽፈን ለሚመለከተው ያቀረብናቸው በርካታ ማመልከቻዎች አሉን፡፡ በአእምሯችን ጓዳ አዋቅረን የተውናቸውም እንደዚሁ፡፡
Teles
ግልፅነት
በትዕግስት ዘሪሁን

ወ/ሮ ቤተልሔም አሸብር ከአምስት ዓመት በፊት ነበር ከእናት ወደ ልጅ የኤች.ኤይ.ቪ ቫይረስ እንዳይተላለፍ የሚደረገውን አገልግሎት ያገኘችው፡፡ "ከመጀመሪያዎቹ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ሴቶች መካከል ሳልሆን አልቀረም" ትላለች፡፡ በወቅቱ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ለእርሷ በምጥ ጊዜ አንድ ኔቨራፒን ከምጥ በኋላ ለልጁ ደግሞ የመከላከያ መድሃኒት ተሰጥቷቸዋል፡፡ በወቅቱ ጡት እንዳታጠባ ተነግሯትም ተግባራዊ አድርጋለች፡፡ ከቫይረሱ ነፃ የሆነ ልጅ እንድታገኝ ያደረጋት ከጤና አገልግሎቱ በተጨማሪ በቤቷና በቤተሰቧ ግልፅነት በመኖሩ እንደሆነ ትናገራለች፡፡
 
Taxi
ማረሻን ማረሻ ማለት
የትራንስፖርት ፈላጊው ቁጥር በጣም በዛብኝ፡፡ በታክሲ፣ በከተማ አውቶቡስ፣ በቤት መኪና፣ በእግር ወዘተ. የሚጓዘው መንገደኛን በመቶኛ ምን ያህል መሆኑን ማስቀመጥ ተሳነኝ፡፡ በርከት ያለው ቁጥር በታክሲና በአውቶቡስ የሚጓጓዘው መንገደኛ ነው፡፡

 
World
Image የምግብ ዋጋ ንረት...
የምግብ ዋጋ ንረት በግብፅ ተቃውሞ አስነሳ

በግብፅ የምግብ ዋጋ ንረት የተቃውሞ ሰልፍ መቀስቀሱንና የዋጋ ንረቱ ፖለቲካዊ ገፅታ መያዙን የቢቢሲ ዘገባ አመለከተ፡፡
 
  • Do You Know ?
    How To Increase Font Size
    You can increase the font size of the website if it appears smaller than normal. Just click the member area link at the top right of this page and the page will slide down. At the top left corner of the page, look for three small buttons. To increase font size, click the button with "+" sign and "-" sign to decrease font size.
  • Tips !
    Tips for Amharic Version
    • Use Internet Explorer version 6 or better
    • Adjust your screen resolution to 1024 X 768
    • Use the font resizer to increase font size if needed
    • Though it is not strictly needed having power geez unicode font could enhance the font rendering in your browser
 

Important Links

Visit Ethiopian Yellow PagesA forum on Dialogue, Democracy & Development