Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Saturday
Jul 04th
Home
Headline
  • Pause
  • Previous
  • Next
1/10
የንብረትን ምንጭ ማሳወቅ...

የንብረትን ምንጭ ማሳወቅ የሚያስገድድ ሕግ ሊፀድቅ ነው
•    ጠበቆች ኦዲተሮችና ደላሎች የደንበኞቻቸውን መረጃዎችን የመስጠት ግዴታ ይጣልባቸዋል

በኃይሌ ሙሉ

በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብንና ሽብርተኝነትና በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተዘጋጀውና ሚኒስትሮች ም/ቤት ባለፈው ሣምንት ያጸደቀው ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ቀረበ፡፡ ረቂቅ አዋጁ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ከየት እንዳመጣ የማስረዳት ግዴታ በማንኛውም ሰው ላይ ተግባራዊ እንዲሆን ይደነግጋል፡፡

 

Read more...
 
Zena
Image የኃይል ቀውሱ

ኢንዱስትሪዎችን እያንኮታኮተ ነው
ባልሰሩበት በወር ከ100ሺህ በላይ የመብራት ክፍያ ይጠየቃሉ

በብርሃኑ ፈቃደ

የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ከጀመረበት ካለፈው ግንቦት ወር 2001 ወዲህ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ የሆኑ ኢንዱስትሪዎችና ፋብሪካዎች ሙሉ በሙሉና በከፊል ሥራ አቁመዋል፡፡ ፋብሪካዎቹ ይህን ለማድረግ የተገደዱት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ኃይል እንዳይጠቀሙ መመሪያ በማስተላለፉ ነው፡፡

 

Editorial
Image "ዝሆን አለመሆኔ እስኪጣራ ድረስስ!"

ጥንቸል

ጥንቸልዋ ሜዳውንም ተራራውንም እያቋረጠች ትሮጣለች፡፡ እየወደቀች እየተነሳች ትቀጥላለች፡፡ ደክሟትም ትንፋሽ አጥሯትም ትሮጣለች፡፡ ትጓዛለች፡፡ አገር አቋርጣም ኬንያ ድንበር ሞያሌ አካባቢ ትደርሳለች፡፡

 

 
Politics
የፀረ-ሽብር ሕግ - ያሸብራል?

በየማነ ናግሽ

የኢትዮጵያ ፓርላማ እየተገባደደ ባለው የሚሌኒየሙ የመጀመሪያ ዓመት ከሶስት በላይ የአገሪቱን የፖለቲካ ምህዳር ድንበር የሚከልሉ አወዛጋቢ ህጎች አጽድቋል፡፡ ፓርላማው ከመበተኑ በፊት ያፀድቀዋል ተብሎ የሚገመተው አንድ ተመሳሳይ ዋጋ የሚሰጠው ህግ አለ፣ የፀረ ሽብርተኝነት ህግ፡፡ አብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አንዳንድ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ቀደም ሲል የፀደቁት ፕሬስን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችንና የተራድኦ ድርጅቶችን የሚመለከቱ ሶስት ህጎች "አፋኝ" ያሉዋቸው ሲሆን፣ የፀረ ሽብር ህግ አዋጅን ደግሞ "አሸባሪ" ነው ሲሉ ይስተዋላሉ፡፡

 

Briefs
ኢብጋህ የዓለም አቀፉ... ኢብጋህ የዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን አባል ሆነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የጋዜጠኞች ኅብረት (ኢብጋህ) የዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች ፌዴሬሽን አባል ሆነ፡፡
 
Business & Economy
Image ዱከምና ኢንቨስትመንት
በዳዊት ታዬ

አቶ ኩማ ኤዴዬ ኤደቻ የ74 ዓመት አዛውንት ናቸው፡፡ ተወልደው ያደጉት ዱከም ከተማ ሲሆን ከመጀመሪያዎቹ የኦሮምኛ የሬዲዮ ፕሮግራም ጋዜጠኞች መካከል አንዱ ናቸው፡፡

Shemach
በተመሳሳይ ስም ማጭበርበር

በናታን ዳዊት

ከገበያ የወጡ የምግብ ዘይት ፋብሪካዎች እንዳሉ እንሰማለን፡፡ የአገር ውስጥ ገበያውን የተቆጣጠሩት በተለያየ ስም የሚገቡ የምግብ ዘይቶች ይገኛሉ፡፡ ቁጥሩ ቀላል የማየባል ሸማች ስላለ ገበያው አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ የዘይት እጠረት እየተፈጠረ ለውጥ የምግብ ዘይት ምርቶች ጥሩ አጋጣሚ እንደሚፈጠር እያየን ነው፡፡

 

 
Interview
Image "ፈንዱ የአርብቶ አደሩን አቅም...

"ፈንዱ የአርብቶ አደሩን አቅም በመገንባት ረገድ ውጤታማ ሆኗል"

የጃፓን ማኅበረሰብ ልማት ፈንድ ፕሮጀክት ባለፉት ሦስት ዓመታት ከ1.8 ሚሊዮን ዶላር በላይ ሲያካሄድ ቆይቶ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ በአርብቶ አደር አካባቢዎች ሰፊ የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በማከናወን አርብቶ አደሩ የሚያቅዳቸውን የልማት ሥራዎች ማስፈፀም የሚችልበትን አቅም እንዲያገኝ እገዛ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

 

Fermata
Image ኦሊምፒክ

ኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ኮሚቴ እ.ኤ.አ. ሰኔ 16 ቀን 1894 ዓ.ም. የእንግሊዝ፣ የአሜሪካ፣ የሶቪየት ሕብረት፣ የሀንጋሪና የግሪክ ተወካዮች በተገኙበት በሳርቦን ዩኒቨርስቲ በተደረገው ኮንግረስ በአማተሪዝም ፍልስፍና ላይ የተገነባ ዓለም አቀፍ ኮሚቴ ሆኖ ተቋቋመ፡፡ የኦሊምፒክ እንቅስቃሴ መሥራች በሆነችው በግሪክ አገር በአቴንስ ከተማ በመሆን በ1896 ተካሄደ፡፡

 

 
Kibur Minister
ክቡር ሚኒስትር

- ትለቃለህ እንዴ?
- ምንድን ነው የምለቀው?
- ከስልጣንህ ከሚኒስትርነትህ
- ለምን? ምነው ጠየቅሽኝ?
- ይህን ጋዜጣ ሳነብ ይኸው "እንደኔ. . . በቃኝ" ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ
- ውድ ባለቤቴ አታስቢ አልለቅም፡፡ ቻው በጧት የሚጀመር ስብሰባ ስላለብኝ ልሂድ

 

Life & Art
Image በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍና ፎክሎር...

በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍና ፎክሎር የዶክትሬት ትምህርት ሊጀመር ነው
በጋዜጣው ሪፖርተር

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሑፍ ክፍል የዶክትሬት ትምህርት መርሐ ግብር ለመጀመር ማቀዱን ገለጸ፡፡

 

 
Social
Image ኢትዮጵያውያን በኢስሊን ናይሮቢ

በምሕረት ሞገስ

በኬንያ ናይሮቢ ኢስሊን በሚባለው ሥፍራ በተለይ አራተኛ መንገድ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ዘልቀው ሲገቡ ኬንያ ሳይሆን ኢትዮጵያ ያሉ እስኪመስልዎት ከአገርዎ ልጆች ጋር ሰላምታ እየተለዋወጡና ኢትዮጵያን ኢትዮጵያን የሚሸቱ ቤቶች፣ ሱቆች፣ እቃዎች እያዩ ይጓዛሉ፡፡የድሮ የነዋይ ደበበ እሸት በላሁኝ የሚለውን ዘፈን አዳምጠው ከየት ነው ብለው ዞር ሲሉ ትኩስ እንጀራ ይሸጣል የሚለውን ያያሉ፡፡ እሱም ብቻ አይደለም በየበሮቹ ላይ ጫት መኖሩን የሚያመላክት የተንጠለጠለ ኮባ ማየት የተለመደ ነው፡፡ በአዲስ አበባ በአራት ኪሎ፣ መርካቶ ወይም ጣሊያን ሰፈር ያሉ እስኪመስሉዎት ግር ያሰኝዎታል በኢስሊን ያለው የኢትዮጵያዊ ብዛትና ኢትዮጵያዊ አኗኗር፡፡

Science & Technology
Image የአሳማ ጉንፋን መድሃኒቱን...

የአሳማ ጉንፋን መድሃኒቱን መለማመዱ ተጠቆመ

ኤክስፐርቶች የአሳማ ጉንፋን (ስዋይን ፍሉ) ወረርሽኝን ለመዋጋት በዋናነት የሚሰጠውን ታሚፍሉ (Tamiflu) መድሃኒት የተለማመደ ስዋይን ፍሉ ማግኘታቸውን አስታወቁ፡፡

 

 
Diaspora
Image የጤና ተቋማትን የኢንፎርሜሽን...

የጤና ተቋማትን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ለማድረግ
በምሕረት ሞገስ

የጤና ተቋማት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን የሚችሉበትንና የሰለጠነውን ዓለም ለተቀላጠፈ የጤና አገልግሎት አሰራር ያበቃውን አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን አቶ ብሩክ ፈቃዱ የቦስተን ቴክ ኮንሰልቲንግ ሥራ አስኪያጅ ገልፀዋል፡፡

 

Youth
Image አለመቀራረብ
በምሕረት አስቻለው

ታላላቆቹ ቀደም ሲል የፋይል ማቀፊያ (box file) እየሰሩ ራሳቸውን ይደግፉ ቤተሰቦቻቸውንም ይረዱ እንደነበር ነግሮናል የአስራ ዘጠኝ ዓመቱ ወጣት እዮብ ካሳሁን፡፡ የሚኖረው አራት ኪሎ 15/16 ቀበሌ ውስጥ ነው፡፡
 
Opinion
የራስን መብትና ጥቅም...

የራስን መብትና ጥቅም መወሰን ነውር ነው

በዛብህ ንጉሡ

በ1954 ዓ.ም. ታህሳስ 28 ቀን የፓርላሜንት አማካሪዎችን ደመወዝ ለመወሰን የወጣን አዋጅ በወቅቱ በነበረው ሕገ መንግሥት ሕግና አሰራር መሰረት ንጉሠ ነገስቱ ያወጁት "በተሻሻለው ሕገ መንግሥታችን በአንቀጽ 34፣ 83 እና 88 የተጻፈውን አይተን የሕግ መምሪያና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤቶቻችን መክረውበት ያቀረቡልንን ተመልክተንና ፈቅደን ቀጥሎ ያለውን አውጀናል" ብለው ነው፡፡ በዚህም መሰረት የእያንዳንዱ የፓርላሜንት አማካሪ የወር ደመወዝ አምስት መቶ ብር እንዲሆን ተወሰነ፡፡ ፓርላሜንቱ ማለት ወይም በወቅቱ ሥራ ላይ በነበረው የ1948 ዓ.ም. ሕገ መንግሥት መሰረት "ፓርላሜንቱ የሕግ መምሪያ ምክር ቤትንና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤትን ይዞ የሚገኝ" ወይም የሚያጠቃልል በመሆኑ የፓርላሜንት አማካሪዎች ደመወዝ አዋጅ ይወጣል በዚህም መሰረት የእያንዳንዱ የፓርላሜንት አማካሪ የወር ደመወዝ አምስት መቶ ብር እንዲሆን የተወሰነ ነው፡፡ ራሱ ፓርላማው ማለትም የሕግ መምሪያና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤቶች መክረውበት ነው፡፡

Letter to Reporter
የማን ጥፋት ነው?

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ ከምርጫ 97 ወዲህ ሥልጣን መልቀቅን በሚመለከት በተለያዩ ጊዜያት ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡፡ ሁሉም ቃለ ምልልሶች ያካሄዱት ግን ከውጭ ሚዲያዎች ጋር ነው፡፡ በአገር ውስጥ ሚዲያ የምንሰማው ማስተባበያውን ነው፡፡

 

 
Women
Image ችሮታ

በትዕግሥት ዘሪሁን

ከፊት ለፊቴ ሁለት ሎተሪ አዟሪዎች ይሄዳሉ፡፡ ሁለቱም በእድሜያቸው ከ30 ዓመት የዘለሉ እንደሆኑ ገመትኩ፡፡ ወንዱ በዱላ እየተመረኮዘ፣ እያነከሰ ይሄዳል፣ ሴቷ ዓይነ ስውር ናት የሚመራት እሱ ነው፡፡ "ዛሬ ለአራሷ ዳቦ የምገዛበት ያህል እንኳን አልሸጥኩም"". ትላለች ማየት የተሳናት ሎተሪ አዟሪ፣ ወሬያቸው ሳበኝ፡፡ ከወሬያቸው እንደተረዳሁት ዓይነ ስውሯ የምታስተዳድራት አራስ ልጅ እንዳለቻት ነው፡፡

 

Temuaget
ጨለምተኛነት ያጠላበት ዴሞክራሲያችን
በይታገሱ ዘውዱ

የቀዝቃዛውን ጦርነት ማብቃት ተከትሎ የምዕራቡ ዓለም የፖለቲካና ኢኮኖሚ ማጠንጠኛ የሆነው የሊብራሊዝም ርዕዮተ-ዓለም ለበርካታ የዓለማችን አገራት ዋነኛ የፖለቲካ መርህና የኢኮኖሚ ተግባራት ማስፈፀሚያ ይሆን ዘንድ ምዕራባዊያን ከምኞት ያለፈ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች ሲያከናውኑ መሰንበታቸው የሚታወስ ነው፡፡
 
Law
የፍትሕ ሚኒስቴርና የፌዴራል...

የፍትሕ ሚኒስቴርና የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አለመግባባት

በሰለሞን ጎሹ

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በቅርቡ በመዝገብ ቁጥር 26127 የተመለከተው ጉዳይ ዋና ጭብጥ ኑሯቸውን አሜሪካን አገር ያደረጉ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ባለትዳር የአሜሪካ ዜጎች በአዲስ አበባ ያላቸው ተንቀሳቃሽ ያልሆነ ንብረት (ቤት) ለማስመለስ ኢትዮጵያዊ ወይዘሮን መክሰስ ላይ ሲሆን፣ ተሰሳሿ ከሳሾቼ ኤርትራዊያን ናቸው፣ ጠበቃቸውም ሕጋዊ ወክልና የላቸውም ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከፍትህ ሚኒስቴር የጠበቆች ዲሲፒሊን ጉባኤ የነሐሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. ውሳኔ ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት ያለው ሲሆን የጠበቃ ውክልናውን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሰነዶችን ከአሜሪካ ሁለት ጊዜ እንዲላኩ ተደርጓል፡፡

 

Zennk
ስለ የጀርመን ንጉሥ

የጀርመን ንጉሥ ታላቁ ፍሬድሪክ የሚባሉት ወደ ጦርነት ሲሂዱ፤ የሰፈሩበትን ቦታ ጠላቶቻቸው እንዳያዩት ብለው አንድ ሰው ስንኳ በድንኳኑ ውስጥ መብራት አያብራ፤ የኔን ትዕዛዝ አፍርሶ መብራት አብርቶ የተገኘውን የሞት ፍርድ እፈርድበታለሁ፤ ብለው አዋጅ ነገሩ፡፡

 

 
Delalaw
ልባችንን ለግንዛቤ ክፍት እናድርግ

ኑሯችንን ለመመርመር ፈለግኩ፡፡ ነገር ግን ከበደኝ፡፡ የአንዳንዶች ሞት ለአንዳዶች ምቾት መሆኑን ሳይ "ሕይወት ረቂቅ" ትሆንብኛለች፡፡ ወደ ማኅበራዊ ሕይወቴና ወደ ድለላው ሙያዬ አተኩራለሁ፡፡ የአንዱ መጥፋት ለሌላው ልማት ሲሆን እታዘባለሁ፡፡ የመታዘቡ ነገር ደግሞ ይበዛብኛል፡፡ የምታዘብ እንጂ የሚታዘቡኝ አይመስለኝም፡፡

 

Teles
"ለሞት ብቻ ጥሩምባ መንፋት ቀረ" በትዕግስት ዘሪሁን

ከተለያዩ ቀበሌዎች 15 ያህል እድሮች ተሰባስበው ጥምረት ፈጥረዋል፡፡ "የእድሮች ጥምረት ለአዲስ ህይወት" የሚል ስያሜ ሰጥተው መንቀሳቀስ ከጀመሩም ቆይተዋል፡፡ ይሄንን የገለፁልን የጥምረቱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ አኑሬ ናቸው፡፡
 
Sport
በኦሊምፒክ ቀን ለትምህርት...  በኦሊምፒክ ቀን ለትምህርት ቤቶች ስፖርት ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ስፖርት ዓለም አቀፍ ተሳትፎ እንዲኖረው ለትምህርት ቤቶች ስፖርት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ፡፡ የኦሊምፒክ ቀንን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፓናል ውይይት ተደርጓል፡፡
Taxi
መፍትሔ

"አዳዲስ ታክሲዎች ለምን አይጨመሩም" አለ አንድ ወጣት በትራንስፖርት እጥረት ተማርሮ፡፡ አሁን አሁን አዳዲስ ታክሲዎች አይታዩም፡፡ ሾፌር ምክንያቱን ያውቅ ይሆናል ብሎ የሾፌሩን መልስ ጠበቀ፡፡ እንደሚጠበቅ ያወቀው ሾፌርም ለመልስ ተዘጋጀ፡፡

 

 
World
Image ሆንዱራስ - የመፈንቅለ መንግሥት ሰለባ በኃይሌ ሙሉ

የሆንዱራስ ፕሬዚዳንት በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከስልጣን መወገዳቸውን ተከትሎ በፕሬዚዳንቱ ደጋፊዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት ተፈጥሯል፡፡ መፈንቅለ መንግሥቱን ከባራክ ኦባማ እስከ ሁጎ ቻቬዝ ድረስ የበርካታ መንግሥታት መሪዎች ያወገዙት ሲሆን፣ ፕሬዚዳንቱ በአስቸኳይ ወደ ስልጣናቸው እንዲመለሱ ጠይቀዋል፡፡
Fere Kenafir
ፍሬከናፍር
"... ፓርላሜንቱ የአባሎቹን ደመወዝ የሚያሳድግ ማናቸውንም ሕግ ያወጣ
 
  • Advertisement
 

Advertisement

Click here to visit our web site

Got an Idea ?

Share your thought and ideas with others on our public forum. Just register here and participate on our new and improved forum. Note that all members of the old version forum have to register again to post on the new version forum.

www.isynci.com