Thu05172012

Go to :English Edition

Back ዜና ዜና አቶ ግርማ ዋቄ በሩዋንዳ ተደራራቢ ሹመት አገኙ

አቶ ግርማ ዋቄ በሩዋንዳ ተደራራቢ ሹመት አገኙ

  • PDF

የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ግርማ ዋቄ የሩዋንዳ መንግሥት የትራንስፖርት ሚኒስቴር በአቪዬሽን ጉዳዮች አማካሪና የሩዋንዳ አየር መንገድ (ሩዋንዳ ኤር) የቦርድ ሊቀመንበር አድርጐ ሾሟቸው፡፡ ባለፈው ሳምንት በሩዋንዳ የጥቂት ቀናት ቆይታ አድርገው ወደ አዲስ አበባ የተመለሱት አቶ ግርማ፣ በመጪው ሳምንት ወደ ኪጋሊ ተመልሰው እንደሚጓዙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአቶ ግርማ ሹመት የሚፀናው ከጥር 23 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ይሆናል፡፡

አቶ ግርማ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ለአፍሪካዊ አየር መንገድ መሥራት የሚያስደስታቸው በመሆኑ ሹመቱን ተቀብለዋል፡፡ አክለውም የሩዋንዳ አየር መንገድ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ተባብሮ በሚሠራበት ሁኔታዎች ላይ እንደሚሠሩ ገልጸዋል፡፡

አቶ ግርማ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለ40 ዓመታት ያህል ካገለገሉ በኋላ ባለፈው ዓመት ጥር ወር ጡረታ ወጥተዋል፡፡ ቀድም ሲል በዲኤችኤልና በገልፍ ኤር በከፍተኛ ኃላፊነት ማገልገላቸው ይታወሳል፡፡ አቶ ግርማ የአዲስ አበባ ሒልተን ሆቴልና የኅብረት ኢንሹራንስ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ናቸው፡፡