Tuesday, May 21st

English Version

Error
  • Error loading feed data.

የአትክልት ተራ ነጋዴዎች በራሳቸው ተነሳሽነት የዋጋ ተመን አወጡ

E-mail Print PDF
User Rating: / 7
PoorBest 

በብርሃኑ ፈቃደ
የአትክልት ተራ ነጋዴዎች በፈቃዳቸው የዋጋ ተመን አወጡ፡፡ በ16 ያህል የምርት ዓይነቶች ላይ የወጣው የዋጋ ተመን ዝርዝር ባለፉት ቀናት በአትክልት ተራ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ነጋዴዎች ሱቆች ላይ ተለጥፎ ሲሠራበት የቆየ ሲሆን፣ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማን መነሻ አድርጐ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተግባራዊ እንደሚደረግ ነጋዴዎቹና የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ባለፈው ዓርብ በሰጡት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

ለአትክልትና ፍራፍሬዎቹ የወጣው የዋጋ ተመን ገበሬውንም እንዳይጐዳ፣ ነጋዴውንም እንዳያስቸግር ተደርጐ የተዘጋጀ እንደሆነ የነጋዴዎቹ ወኪሎች ገልጸው፣ ዋጋ መለወጥ በሚያስፈልግበት ወቅትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከር የሚሻሻል እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡