"ለሁላችን አስፈላጊ የኾነ ጉባኤ ነው፡፡ ደዌያችን መለያየት ነው፤ መንቀፍ፣ ማቃለል ከክርስትና ውጭ የኾነ ነገር ነው፤ መስመሩን ጠብቀን መሄድ አለብን፡፡ በፍቅር፣ በመከባበር ሳይሆን፤ መነቃቀፍና ጥላቻ ያለበት ነገር ብዙ አልፏል፡፡ ተፋቀሩ፤ ተዋደዱ፤ እንላለን፡፡"
ፍሬ ከናፍር - Fere Kenafir
ፍረ ከናፍር
ፍሬከናፍር
ፍሬከናፍር
" . . በየነ ጴጥሮስ ተሳስቷል እንበል፤ ስዬ ተሳስቷል እንበል፤ ቡልቻ ተሳሳቱ እንበል፤ መረራ ተሳስቷል እንበል፡፡ መድረክ ቢያሸንፍ፤ በየነ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ስዬ መከላከያ ሚኒስትር፣ መረራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ቡልቻ ፕሬዚዳንት ቢሆኑ፤ እነዚህን ሰዎች እንዴት ትጠይቃቸዋለህ?"
ፍሬከናፍር
"እናንተ ዛሬ እናት አገራችሁን ወክላችሁ፣ በጣም እሩቅ አገር በመሄድ ወታደራዊ ግዳጃችሁን እንድትወጡ የተደረገው፣ በአገራችን እንደምናውቀው ለነጻነታችን ባደረግነው ተጋድሎ ብቻ ተወስነን የምንቀር ሳይሆን፤ የእያንዳንዱን ሰው ነጻነት ሊያስከብር፣ በጣም ለተቀደሰ ዘመናዊና ዓለም አቀፋዊ ፕሪን ስፕል የምንደግፍ በመሆኑ፣ አገራችሁንና ሕዝባችሁን ወክላችሁ እንድትዘምቱ ተደርጓል፡፡"
ፍሬከናፍር
"... በኢትዮጵያ ምርጫ በመጣ ቁጥር፣ አገራችንን በቀለም አብዮት ለማተራመስ የሚደረገው ሙከራም ሆነ፣ ኢትዮጵያን ለውጭ ኃይሎች ባደሩ ተላላኪዎች እንደልብ የማሽከርከር ዕድል ከቶውንም አይሰምርም፡፡"
የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት፣ ለሂውማን ራይትስ ዎች ሪፖርት ምላሽ በትናትናው ዕለት ካወጣው መግለጫ የተወሰደ፡፡
ፍሬከናፍር
"በምርጫውና በውድድሩ ሂደት ሰዶ ማሳደድ ውስጥ መግባት አንፈልግም፡፡ ይኽን ወንጀል ፈጽመሃል፤ ይኽን ሕግ ጥሰሃል፤ ይኽን አድርገሃል፤ ብለን ሰዶ ማሳደድ ውስጥ መግባት አንፈልግም፡፡ የምርጫውን ገጽታ ያበላሻልና፡፡ በተቻለ መጠን አሁን ታግሰን፣ ማስረጃውን ሰብስበን፣ በማስረጃው ላይ በመመሥረት ከምርጫው በኋላ ክስ ለመመሥረት እንሞክራለን"
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ መጋቢት 9 ቀን 2002 ዓ.ም ስለወቅታዊ ጉዳዮች ለሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች ከተናገሩት
Page 5 of 7



"ሕዝባችንን አስርበን የጦር መሣሪያ መግዛት ራስን እንደማጥፋት ይቆጠራል"