"ጠጅ መጠጣትና ጥሬ ሥጋ መብላት ሀበሻነቴን የሚያስነሣ ይመስለኛል"
ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ "የዘመን ትሩፋት" በተሰኘውና የካቲት 27 ቀን 2002 ዓ.ም. በተመረቀው የሕይወት ታሪካቸው ዘጋቢ ፊልም ውስጥ የተናገሩት
"ጠጅ መጠጣትና ጥሬ ሥጋ መብላት ሀበሻነቴን የሚያስነሣ ይመስለኛል"
ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ "የዘመን ትሩፋት" በተሰኘውና የካቲት 27 ቀን 2002 ዓ.ም. በተመረቀው የሕይወት ታሪካቸው ዘጋቢ ፊልም ውስጥ የተናገሩት
"ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም፡፡ አንተም እስካሁን አላስቀየምኸኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ፡፡ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለሚስትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በኀዘን እርዳኝ፡፡
"በታሪክ አካሄድ ያየን እንደሆነ ሕያዋን ናቸው እንጂ ሙታን አይደሉም፡፡ እንዴ" አለ እየተባለ እኮ ሙቶ የሚኖር ሕዝብ ሞልቷል፡፡"
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በቅርቡ በቤይሩት በአውሮፕላን አደጋ ሕይወታቸውን ባጡ ኢትዮጵያውያን ሥርዓተ ቀብር የካቲት 7 ቀን 2002 ዓ.ም. በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሲፈጸም ያሰሙት ቃለ ምዕዳን፡፡
"ወደፊትም ቢሆን ተጨባጭ የሆነ ነገር ይሠራል ብዬ አላምንም፡፡ ምክንያቱም በሊቀመንበርነት ጊዜዬ የተማርኩት ነገር ቢኖር የአፍሪካ የፖለቲካ መሪዎች ብቃትም ሆነ ቁርጠኝነት የላቸውም"፡፡
የሊቢያው ፕሬዚዳንት ኮሎኔል ሙዓመር ጋዳፊ ጥር 24 ቀን 2002 በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነትን ለማላዊው ፕሬዚዳንት ባስረከቡበት ወቅት ያደረጉት ንግግር፡፡
"ቸር አምላክ፣ የሙታኑን ነፍስ በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በበረራ ደኅንነቱና በአገልግሎት ጥራቱ የአፍሪካ ኩራት ነው""
ጥር 16 ቀን 2002 ዓ.ም. ለ17 አጥቢያ በሜዲትራኒያን ባሕር ላይ የወደቀውን የኢትዮጵያ አውሮፕላን ተከትሎ፣ አንድ አስተያየት ሰጪ ለሲቢሲ ኒውስ ከተናገሩት የተወሰደ፡፡
"ታላቁን የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባመዛኙ የውጭ አገር ሰዎች ጽፈውት ለኢትዮጵያውያን ኅሊና የማይቆረቁር ውጤት ይገኛል፤ ማለት ዘበት መኾኑን በኅሊናችን መቋጠር ግዴታችን ይኾናል፡፡
"ያኔም እንደተናገርኩት ግመሎች ውሃ የሚጠጡበት ካልሆነ በስተቀር ዓሰብ አገልግሎት የሚሰጥ አልሆነም፡፡"
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ በታህሣሥ 1 ቀን 2002 ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የአሰብ ወደብን በሚመለከት ተጠይቀው ከመለሱት
"የመንግሥት ሚዲያዎች ሁሉንም ፓርቲዎች በእኩልነትና በፍትሃዊነት በማገልገል ያደረጉት እንቅስቃሴ በወቅቱ ምርጫውን የታዘቡ የውጭ ታዛቢዎች ሳይቀሩ የመሰከሩለት ሃቅ ነው"
Page 6 of 7