አጫጭር ዜናዎች - Briefs
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኮሪያን ድጋፍ ጠየቁ
ኢትዮጵያ ተግባራዊ እያደረገችው ያለችውን የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት የኮሪያ ሪፐብሊክ ትብብር እንድታደርግላት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ መጠየቃቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
Read more...
በብራዚል 12 ተማሪዎች ተገደሉ
ባለፈው ሐሙስ ብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ በሚገኝ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ አንድ የታጠቀ ግለሰብ በከፈተው ተኩስ 12 ተማሪዎችን ገደለ፡፡
Read more...
የጐማ ዛፍ ምርትን ለማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ ተጀመረ
በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ የአገሪቱን የጐማ ዛፍ ምርት ከሦስት ሺሕ ቶን በላይ ለማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ የጐማ ዛፍ ልማት ናሽናል ኒኩለስ ፕሮጀክት ማስታወቁን ዋልታ ዘገበ፡፡ የኢትዮጵያ የጐማ ዛፍ ልማት ናሽናል ኒኩለስ ፕሮጀክት በ2009 ዓ.ም. 3,275 ቶን የጐማ ዛፍ ምርት ለገበያ ያቀርባል፡፡
Read more...
የተመድ አውሮፕላን ተከስክሶ 32 ሰዎች ሞቱ
በዲሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ ኮንጎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) አውሮፕላን ተከስክሶ በውስጡ ከነበሩት 33 ሰዎች 32ቱ ሲሞቱ አንዱ ብቻ መትረፉን የዘገበው ሲኤንኤን ነው፡፡
Read more...
ለዓለም አቀፉ የኤችአይቪ/ኤድስ ጉባዔ ስድስት ሚሊዮን ዶላር ያስፈልጋል
ኢትዮጵያ ለምታስተናግደው ዓለም አቀፍ የኤችአይቪ ኤድስና በግብረ ሥጋ ለሚተላለፉ በሽታዎች 16ኛ ጉባዔ ስድስት ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ ኢዜአ ዘገበ፡፡
Read more...
ኔቶ የሊቢያ አማፅያንን አስጠነቀቀ
ኔቶ የሊቢያ አማፅያን በንጹኅን ዜጎች ላይ ምንም ዓይነት ጥቃት እንዳያደርሱ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን የዘገበው ኒው ዮርክ ታይምስ ነው፡፡
Read more...
የሰባት የልማት ድርጅቶችና አክሲዮን ማኅበራት ጨረታ ተከፈተ
የፕራይቬታይዜሽንና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ በተያዘው የበጀት ዓመት ለሁለተኛ ጊዜ ወደግል ለማዞር ያቀረባቸው ሰባት የልማት ድርጅቶችና አክሲዮን ማኅበራት ጨረታ በይፋ መከፈቱን አዲስ ዘመን ዘገበ፡፡
Read more...
ጣሊያን ስደተኞችን ላለመቀበል ወደቧን ዘጋች
ጣሊያን በመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች በተነሳው ብጥብጥ ሳቢያ የስደተኞች ቁጥር ከአቅሟ በላይ ስለሆነባት ወደቧን መዝጋቷን አልጄዚራ ዘግቧል፡፡
Read more...
ዘጠና ሦስት ኢትዮጵያውያን ከሊቢያ ወደ ቱኒዚያ ተጓጓዙ
የኢትዮጵያ መንግሥት ሊቢያ የሚኖሩ ዜጐቹን ደኅንነት ለመጠበቅ እያደረገ ባለው ጥረት 93 ዜጐቹን ከሊቢያ ወደ ቱኒዚያ ማስወጣቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በላከው መግለጫ አስታወቀ፡፡
Read more...
በማይናማር የመሬት መንቀጥቀጥ ከ65 በላይ ሰዎች ሞቱ
በማይናማር በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ከ65 በላይ ሰዎች መሞታቸውንና ከ110 በላይ መቁሰላቸውን የዘገበው ሲኤንኤን ነው፡፡
Read more...
More Articles...
Page 1 of 28


