Sunday, May 19th

English Version

Error
  • Error loading feed data.

በህግ አምላክ - Law

"የመረጃ ነፃነት እና የማወቅ መብት" በሚል የፕሬስ ቀን ተከበረ

E-mail Print PDF

 

Freedom for informationበዮሴፍ ሳህለሥላሴ

የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን ሆርን ኦፍ አፍሪካ ፕሬስ ኢንስቲትዩት እና የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በጋራ፣ ሚያዝያ 28 ቀን 2002 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል ባዘጋጁት የአንድ ቀን ዐውደ ጥናት ..የመረጃ ነፃነት እና የማወቅ መብት.. በሚል መሪ ቃል ተከበረ፡፡

Read more...

ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ እና የሄግ ኮንቬንሽን

E-mail Print PDF

ሕጻናት የነገ አገር ተረካቢ እንደመሆናቸው መጠን የሁሉንም እንክብካቤ እና ድጋፍ ይሻሉ፡፡ የሕጻናትን መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ በዓለም አቀፍ እና በአህጉራዊ ደረጃ የሕግ ማዕቀፎች ተዘጋጅተዋል፡፡

Read more...

የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ግድፈቶች በሕክምና መስጫ ተቋማት

E-mail Print PDF
User Rating: / 2
PoorBest 

(በሙላት ገ/ሕይወት ገዛኸኝ)

በአገራችን ውስጥ የሕክምና ውልና አሉታዊ ውጤቶቻቸውን በተመለከተ እንደ ሌሎቹ የውል ዓይነቶች በኅብረተሰባችን (በታካሚው፣ በሐኪሙና በተቋማቱ) ዘንድ እውቅና አግኝቶ ውሉ በተሟላ ሁኔታ አይሠራበትም፤ የውሉ ውጤት አሉታዊ ሆኖ ቢከሠትም፣ በተዋዋዮቹ ዘንድ ትኩረት አይሰጥበትም፤ በሕክምና አገልግሎት ሰጪው (ሐኪሙም ሆነ ተቋሙ) አገልግሎት የሚሰጠው ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ልምድ መሠረት ባደረገ አኳኋን እንጂ በፍ/ብ/ሕጉ ስለ ሕክምና ሕግ፣ በሕክምና ሕግ ድርሳናትና በሙያ ሥነ ምግባሩ ደንብ ድንጋጌ መሠረት አይመራም ብሎ መግለጽ ማጋነን አይሆንም፡፡

Read more...

የዋስትና ውል መሠረታዊ ጽንሰ ሐሳብ

E-mail Print PDF

በጋዜጣው ሪፖርተር

በማኅበራዊ ግንኙነት ውስጥ የዋስትና ውል ማድረግ የተለመደ ተግባር ነው፡፡ የዋስትና ውል ማለት ሁለት ሰዎች ባደረጉት የባለገንዘብነትና የባለዕዳነት ግዴታ ውስጥ ከእነርሱ ውጪ የሆነ ሦስተኛ ሰው ባለዕዳው ዕዳውን በሙሉ ወይም በከፊል ያለከፈለ እንደሆነ ወይም ግዴታውን በአግባቡ ያልተወጣ ከሆነ እኔ በእርሱ ሥፍራ ሆኜ ገንዘቡን እከፍላለሁ ወይም ግዴታውን እወጣለሁ በማለት ለባለገንዘቡ ማረጋገጫ የሚሰጥበት ውል ነው፡፡

Read more...

የተከራካሪ ወገኖች በቀጠሮ ቀን አለመቅረብ የሚያስከትለው ሕጋዊ ውጤት፡-

E-mail Print PDF

በጋዜጣው ሪፖርተር

በፍርድ ሒደት ውስጥ፣ በቀጠሮ ቀን የከሳሽ፣ ተከሳሽ ወይም ደግሞ ወኪሎቻቸው በቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት መገኘት አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ በተከራካሪዎቹ መካከል አግባብ ያልሆነ መጉላላት እንዳይፈጠር ከፍተኛ እገዛ ያደረጋል፡፡ ከተከራካሪዎቹ አንዱ ያለ በቂ ምክንያት በቀጠሮ ቀን ፍርድ ቤት ሳይቀርብ ቢቀር በሌላኛው ወገን ላይ አላስፈላጊ እንግልት እንዲደርስ ያደርጋል፡፡

Read more...

የተከሰሱ ሰዎች መሠረታዊ መብቶች በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት

E-mail Print PDF

የተከሰሱ ሰዎችን በተመለከተ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግሥት የተለያዩ መሠረታዊ መብቶች ተቀምጠዋል፡፡ እነዚህ መብቶች በሕገ መንግሥቱ አንቀፅ 20 በዝርዝር ይገኛሉ፡፡ ይኸውም፡-
-  በመደበኛ ፍርድ ቤት ለሕዝብ ግልጽ በሆነ ችሎት የመዳኘት መብት፣
- ክሱ በቂ በሆነ ዝርዝር እንዲነገራቸው እና ክሱን በጽሑፍ የማግኘት መብት፣

Read more...

የሕጻናትን ደህንነት የተመለከተ የሰበር ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔ

E-mail Print PDF

በጋዜጣው ሪፖርተር

ሕጻናት ልዩ ትኩረትና ከለላ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ይህም በመኾኑ የሕጻናት መብትን ለማስጠበቅ በዓለም አቀፍ፣ በአኅጉር እና በብሔራዊ ደረጃ የሚገኙ ተቋማት በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡ ተቋማቱ በየተዋረዳቸው ልዩ ልዩ ሕግጋትን አውጥተዋል፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ እ.ኤ.አ በ1989 የወጣው ዓለም አቀፍ የሕጻናት መብቶች ኮንቬንሽን በዋናነት ይጠቀሳል፡፡ በአኅጉር ደረጃ እ.ኤ.አ በ1990 የወጣው የአፍሪካ የሕጻናት መብቶች እና ደኅንነት ቻርተርም ተጠቃሽ ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥትም በአንቀጽ 36 እና በሌሎች ድንጋጌዎች ላይ የሕጻናትን መብቶች የተመለከቱ ድንጋጌዎችን አካትቷል፡፡

Read more...

ሰብአዊ መብትን በአምሳለ ፍ/ቤት ውድድር ማስተማር

E-mail Print PDF

በሰለሞን ጎሹ

የሰብአዊ መብቶች አጠባበቅ ጉዳይ ለአንድ አካል ብቻ የሚተው እንዳልሆነ የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የሙያ ማኅበራት፣ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አማካኝነት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ማኅበረሰቡን ሰብአዊ መብቶችን በአምሳለ ፍ/ቤት ውድድር የማስተማር ጥረትም ርእሰ ጉዳዩ ዘርፈ-ብዙ ተዋናዮች እንዳሉት ያሳያል፡፡

Read more...

በአደጋና በቸልተኛ የወንጀል ድርጊት መካከል ያለውን ልዩነት መሠረት ያደረገ የሰበር ሰሚ ውሳኔ

E-mail Print PDF

በወንጀል ሕግ አንቀጽ 57 መሠረት አንድ ሰው በወንጀል ጥፋተኛ የሚባለው ድርጊቱን አስቦ ወይም በቸልተኝነት ያደረገ እንደሆነ ነው፡፡ ይሁን እንጂ የፈጸመው ድርጊት በሕግ የሚያስቀጣ ቢሆንም ምንም ጥፋት ሳያደርግ ወይም ከአቅም በላይ በሆነ ኃይል ምክንያት ወይም በድንገተኛ  አጋጣሚ ነገር የተፈጸመ ወይም የደረሰ ሆኖ ሲገኝ በወንጀል ሕግ ሊፈረድበት እንደማይገባ የወንጀል ሕጉ በአንቀጽ 57(2) ይደነግጋል፡፡

Read more...

የምግብ መብት መሠረታዊ የሰብዓዊ መብት ነው

E-mail Print PDF

(በጋዜጣው ሪፖርተር)

የምግብ መብት የሰብዓዊ መብት ነው፡፡ ይህ መብት የሚጠብቀው የሰዎችን በክብር መኖር፣ ከረሀብ ነፃ የመሆን፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እና የተመጣጠነ ምግብን ማግኘትን ነው፡፡ የምግብ መብትን ማረጋገጥ የችሮታ ጉዳይ አይደለም ነገር ግን የሁሉንም ሰዎች ራሳቸውን በክብር የመመገብ መብት ማረጋገጥ ነው፡፡

Read more...

Page 8 of 10