Saturday, May 25th

English Version

Error
  • Error loading feed data.

ዜና- News

የግል ድርጅቶች ጡረታ ፈንድ የፈጠረው ብዥታ

E-mail Print PDF
User Rating: / 31
PoorBest 

መንግሥት ያዘጋጀውን የግል ድርጅቶች የጡረታ ፈንድ ረቂቅ አዋጅ ሰሞኑን ለተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ረቂቅ አዋጁ ከሰኔ 2002 ዓ.ም. በፊት ፕሮቪደንት ፈንድ ያቋቋሙ የግል ድርጅቶች ከፈለጉ ብቻ በጡረታ ፈንድ እንደሚታቀፉ ይገልጻል፡፡ በተጨማሪም ረቂቅ አዋጁ ከአሥር ዓመት ያነሰ ጊዜ ያገለገለ ሠራተኛ ድርጅቱን ሲለቅ ያዋጣው ገንዘብ አይመለስለትም ይላል፡፡ ከሃያ ዓመት በታች ያገለገለ ሠራተኛ እንዲሁ ሲለቅ ራሱ ያዋጣው ገንዘብ ብቻ እንደሚመለስለት ረቂቅ አዋጁ ያትታል፡፡ ይህ ረቂቅ አዋጅ የፈጠረውን ብዥታ የሚያሳየውን ዘገባ በቢዝነስ ገጽ ላይ ይመልከቱ፡፡

 

የግብፅ የጦርነት እንቅስቃሴ ትኩረት ለማስቀየር መሆኑን መንግሥት ገለጸ

E-mail Print PDF
User Rating: / 30
PoorBest 

- ሱዳን በቅርቡ ከግብፅ ጐራ ልታፈነግጥ ትችላለች

በዘካሪያስ ስንታየሁ

አዲሱ የግብፅ መንግሥት በዓባይ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ሊነሳ በሚችል ግጭት ምክንያት ሠራዊቱን በተጠንቀቅ እንዲቆም ቢያዝም፣ የግብፅ የጦርነት እንቅስቃሴ ትኩረት ለማስቀየር መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታወቀ፡፡

Read more...

የግብፅ ኩባንያ በቤኒሻንጉል ከፍተኛ የወርቅ ክምችት አገኘ

E-mail Print PDF
User Rating: / 11
PoorBest 

በውድነህ ዘነበ

የግብፁ የማዕድን ኩባንያ አስኮም የሚሌኒየም ግድብ በሚገነባበት ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ ባካሄደው የወርቅ ፍለጋ ከፍተኛ የወርቅ ክምችት ማግኘቱ ተረጋገጠ፡፡

Read more...

‹‹በኢትዮጵያ ዓመፅ ቢነሳ ባለቤቱ ሕዝቡ እንጂ ፓርቲዎች አይደሉም›› አንድነት ፓርቲ

E-mail Print PDF
User Rating: / 14
PoorBest 

- መድረክ ዛሬ በመቀሌ ለጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይቀሰቅስ መከልከሉን ገለጸ

በየማነ ናግሽ

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ሰሞኑን ‹‹ሽብርና አመፅን ከሚቀሰቅሱ መካከል›› ያሉዋቸውን የአንድነት የፓርቲ አባላት ማስጠንቀቃቸውን ተከትሎ፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ በኢትዮጵያ ሕዝባዊ አመፅ የሚቀሰቀስ ከሆነ የእንቅስቃሴው ባለቤት ራሱ ሕዝቡ እንጂ ፓርቲዎች አይደሉም አለ፡፡

Read more...

የአዋሽ ባንክ ተከሳሾች ከአገር እንዳይወጡ እግድ ተጣለባቸው

E-mail Print PDF
User Rating: / 3
PoorBest 

- እያንዳንዳቸው በአሥር ሺሕ ብር ዋስ ተለቀቁ

በታምሩ ፅጌ

የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማኅበር ፕሬዚዳንት የነበሩትን አቶ ለይኩን ብርሃኑን ጨምሮ አሥሩም ተጠርጣሪዎች ከመጋቢት 28 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ ከአገር እንዳይወጡ በፍርድ ቤት እግድ ተጣለባቸው፡፡

Read more...

ባንኮች የስምንት ወራት ሰነድ ግዥ ውዝፍ መክፈል ጀምሩ ተባሉ

E-mail Print PDF
User Rating: / 1
PoorBest 

በአስራት ሥዩም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ቀደም ሲል በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረውን የብድር ገደብ በማንሳት የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ መመሪያ ካወጣ በኋላ፣ ባንኮቹ ካለፈው ሐምሌ 2002 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ የካቲት 2003 ዓ.ም. ድረስ ለሰጡት ብድር 27 በመቶ ውዝፍ የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ እንዲከፍሉ ታዘዋል፡፡

Read more...

የሸራተን አዲስ የመጀመሪያዎቹ ተነሺዎች ቤታችንን ልንነጠቅ ነው አሉ

E-mail Print PDF
User Rating: / 3
PoorBest 

በታምሩ ጽጌ

ሼክ መሐመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ሸራተን አዲስን ከመገንባታቸው በፊት በነፃ ቤት ሠርተው እንደሰጧቸውና ይዞታውም የእነሱ እንደሆነ በወቅቱ እንደነገሯቸው የሚገልጹት ሆቴሉ ከተሠራበት ቦታ ላይ ተነስተው ወደ ሲኤምሲ የተዛወሩ በርካታ ነዋሪዎች፣ የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤቱ የራሱ መሆኑን በመግለጽ ሊነጥቃቸው መሆኑን ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

Read more...

የሚሌኒየም ቦንድ ገበያው ደርቷል

E-mail Print PDF
User Rating: / 1
PoorBest 

በውድነህ ዘነበ

በዓባይ ወንዝ ላይ ለሚገነባው የሚሌኒየም ግድብ የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን የተጀመረው የሚሌኒየም ቦንድ ሽያጭ በአገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ትኩረት እየሳበ ሲሆን፣ ግዢውን ለመፈጸም በርካታ ሰዎች የኢትዮጵያ ልማት ባንክንና የኢትዮጵያ ንግድ ባንኮችን እያጨናነቁ ነው፡፡

Read more...

የደቡብ ኮርያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በግብርና ልማትና በማዕድን ፍለጋ ሊሠማሩ ነው

E-mail Print PDF

በየማነ ናግሽ

የደቡብ ኮርያ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በግብርና ልማትና በማዕድን ፍለጋ ኢንቨስትመንት ሊሠማሩ መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

Read more...

አያት አክሲዮን ማኅበር የመከላከያ ምስክሮቹን ማሰማት ቀጥሏል

E-mail Print PDF
User Rating: / 1
PoorBest 

በታምሩ ጽጌ እና በለምለም ፀጋይ

የአያት አክሲዮን ማኅበር ዋና ባለድርሻና ሥራ አስኪያጁ አቶ አያሌው ተሰማ፣ ዶ/ር መሐሪ መኮንንና አቶ ጌታቸው አጐናፍር መጋቢት 29 ቀን 2003 ዓ.ም. ካቀረቧቸው አምስት የመከላከያ ምስክሮች አራቱን አሰሙ፡፡

Read more...

Page 1 of 148

  • «
  •  Start 
  •  Prev 
  •  1 
  •  2 
  •  3 
  •  4 
  •  5 
  •  6 
  •  7 
  •  8 
  •  9 
  •  10 
  •  Next 
  •  End 
  • »