የገዢው ፓርቲ አባል ድርጅቶች የድርጅቶቻቸውን አመራሮች ሹም ሽር አጠናቀዋል፡፡ ክልሎችም የአስተዳደር መሪዎችን ሹመትና ምደባ እያጠናቀቁ ናቸው፡፡
ከአዲስ ተሿሚዎች አዲስ ሕዝባዊ መንፈስ እንጠብቃለን
ተቃዋሚ ፓርቲዎችም አስቸኳይ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ያስፈልጋቸዋል!!
ስለ አገራችን ዕድገት በምናስብበት ጊዜ ገዢው ፓርቲ ወይም መንግሥት ምን እያደረገና እያሳካ ነው ብለን ብቻ ማሰብ ተገቢ አይሆንም፡፡ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት፡፡
ዝምታ ወርቅ አይደለም! መደማመጥ ግን ወርቅ ነው!
የተወለድንበትም፣ ያደግንበትም፣ የምንኖርበትም አባባል፣ ‹‹ዝምታ ወርቅ ነው›› የሚል ነው፡፡ ዝም የሚል፣ የማይናገርና የማይቃወም ሰው አዋቂ፣ ጠባይ ያለው፣ ትዕግስተኛ፣ አስተዋይ፣ ምራቁን የዋጠና ሁሉንም ነገር ለፈጣሪው የሚተው እየተባለ ሲወደስ፤ በአንጻሩ ደግሞ የሚናገር፣ የሚቃወም፣ ትክክል አይደለም የሚልና አልስማማም የሚል ደግሞ ነገረኛ፣ እልኸኛ፣ ለፍላፊ፣ ጯሂ፣ አዋቂ ነኝ ባይ፣ እንጣጥ እንጣጥ የሚል፣ ሰውን የሚንቅ፣ ነገረኛ፣ ጉረኛ እየተባለ ዘወትር ሲወቀስና ሲወገዝ እንሰማለን፡፡
ኧረ . . . እንነጋገር!
‹‹መወያየት መልካም›› የሚለው የተለመደ አባባል፣ አስቀድሞ ውይይት ከተደረገና መነጋገር ካለ አለመግባባት ሳይኖር ሥራ ሊካሄድ ይችላል፤ ውጤትም ይገኝበታል ለማለት የምንጠቀምበት አገላለጽ ነው፡፡
የተሳካው ይጠናከር! ያልተጠናቀቀው ይጠናቀቅ!
ኢሕአዴግ በአዳማ ከተማ ሲያካሄድ የነበረውን ስምንተኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን አጠናቋል፡፡ ድርጅቱን የሚመሩ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር፣ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትና የምክር ቤት አባላትንም አስመርጧል፡፡
አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ለማሸነፍ ውስጥን በቅንነት መፈተሽ!
ከዛሬው ዕለት ጀምሮ ኢሕአዴግ በአዳማ ከተማ ስምንተኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን እያካሄደ ነው፡፡ ካለፉት ጉባዔዎች የሚለየው ነገር አለ ወይ? ልዩ ትኩረት ያስፈልገዋል ወይ? ጉባዔ፣ ጉባዔ ነው?
የፍትሕ፣ የሰብዓዊ መብት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሰላም፣ የፀረ ሙስና፣ የዴሞክራሲና የልማት ዓመት ያድርግልን!
አዲስ ዓመት ሲመጣ መልካም መመኘት የተለመደ ቢሆንም፣ አዲስ መጪን ዓመት የፍትሕ፣ የሰብዓዊ መብት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ዓመት ያደርግልን ብለን ስንመኝ ግን ተራ ምኞት ሳይሆን፤ መማፀንም ጭምር ነው፡፡
በአስተሳሰባቸው ላይ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን የማያመጡ ሰዎች በኅብረተሰቡ ላይ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ሊያመጡ አይችሉም! !
ኢትዮጵያ፣ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ትፈልጋለች? ያስፈልጋታልን? የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ይናፍቃልን? መልሱ ግልጽና ግልጽ በሆነ መንገድ ‹‹አዎን›› ነው፡፡ ያውም በአስቸኳይ!
ብዥታን፣ ስጋትንና ጥርጣሬን ለማስወገድ፡- እንነጋገር! እንደማመጥ!
በሕዝብና በመንግሥት መካከል መነጋገርና መደማመጥ ካለ፣ ከባድ ችግርም ይቀላል፤ ይቃለላል፤ ይፈታል፡፡ ብዥታና ስጋት፣ ጥርጣሬም አያስከትልም፡፡
Page 7 of 17


