Wednesday, September 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የአስታራቂነት ሚናዋን እንድትወጣ ሲኖዶሱ ለመንግሥት ጥያቄ አቀረበ

ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የአስታራቂነት ሚናዋን እንድትወጣ ሲኖዶሱ ለመንግሥት ጥያቄ አቀረበ

ቀን:

በኢትዮጵያ በቀጣይ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭት እንዲወገድ ለማድረግ የአስታራቂነት ሚናዋን ለመወጣት እንድትችል፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በይፋ ጠየቀች፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱ ይህንን ጥያቄ ለፌዴራል መንግሥት መላኳን ያስታወቁት ፓትርያርኩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ለሁለት ሳምንት ያካሄደውን ጉባዔ መጠናቀቁን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡

ፓትርያርኩ ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ ሲኖዶሱ ለአገርና ለሕዝብ ሰላም መገኘት፣ ለተሰደዱና ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ መረጋጋትና ወደ ቀዬአቸው መመለስ ጦርነትና የሰላም ዕጦት በሚወገድበት ሁኔታ በመምከርና አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ውሳኔዎችን ማሳለፉ አስታውቀዋል፡፡

‹‹በቀጣይ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭት ተወግዶ አጠቃላይ ሰላም በሚሰፍንበት መንገድ ተነጋግሮ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት እንዲቻል፣ ቤተ ክርስቲያናችን የአስታራቂነት ሚናዋን መጫወት እንድትችል ለማድረግ ለፌዴራል መንግሥት ጥያቄ እንዲቀርብ ተደርጓል፤›› ብለዋል፡፡

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተከሰተው የሰላም ዕጦት ምክንያት በቤተ ክርስቲያኒቱ፣ በካህናትና በምዕመናን ላይ የደረሰውና እየደረሰ ያለው የሰው ሕይወት መጥፋትን በአሳሳቢነቱ የዘረዘሩት ፓትርያርኩ የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል፣ የበዓል ማክበሪያ ቦታዎች መነጠቅ አስመልክቶ ጉባዔው መነጋገሩን፣ አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ፣ በቀጣይም በመንግሥት በኩል አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግ ለፌዴራልና ለክልል መንግሥት አካላት ጥያቄው እንዲቀርብ ተደርጓል ብለዋል፡፡

አክለው በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የደረሰውን ችግር በዓይነትና በቁጥር ተለይቶ ለመንግሥት አካላት መቅረቡንም ሳይገልጹ አላለፉም፡፡

በዓመት ሁለት ጊዜ ጉባዔውን የሚያካሂደው ቅዱስ ሲኖዶስ ሁለተኛውን ጉባዔ ከግንቦት 9 እስከ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ማከናወኑ ታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...