Friday, September 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የተተከሉ ችግኞች 84 በመቶ የሚያድጉ መሆኑ ተገለጸ

በአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ የተተከሉ ችግኞች 84 በመቶ የሚያድጉ መሆኑ ተገለጸ

ቀን:

‹‹አረንጓዴ አሻራ›› በማለት ከአራት ዓመታት በፊት በተጀመረው ችግኝ የመትከል ንቅናቄ ትናንት ሰኔ 14 ቀን 2014 ዓ.ም. የተተገበረ ሲሆን፣ የተተከሉ ችግኞች የመዳንና የማደግ መጠን ወደ 84 በመቶ እንደሚጠጋ ተገለጸ፡፡

በአራተኛው አረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ማስጀመርያ ፕሮግራም ላይ የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፣ ንቅናቄው ሲጀመር በአራት ዓመታት ለመትከል ታስቦ ከነበረው 20 ቢሊዮን ችግኞች ውስጥ እስካሁን በተደረጉት ሦስት ዓመታት 18 ቢሊዮን ችግኞችን መትከል ተችሏል፡፡

በዚህ በአራተኛው ንቅናቄም ሰባት ቢሊዮን ችግኞች ለመትከል እንደታሰበ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ በዚህም አጠቃላይ የአራት ዓመቱ ችግኝ ተከላ ሥሌት ወደ 25 ቢሊዮን የሚጠጋ እንደሚሆን አክለዋል፡፡

‹‹አሁን በክልሎች ከተዘጋጁት ሰባት ቢሊዮን ችግኞች ውስጥ 52 በመቶ የሚሆኑትን በአግሮ ፎረስትሪ ምድብ ውስጥ የሚካተቱ ሲሆን፣ 47 በመቶ ደግሞ በደንነት (ፎረስት) ብቻ ይሆናሉ፡፡ ቀሪው አንድ በመቶ ደግሞ ማስጌጫ ተክል (አርኖ ሜንታል) ውስጥ የሚካተት ነው፤›› በማለት አቶ ዑመር ገልጸዋል፡፡

በዚህ የችግኝ ተከላ ንቅናቄ ውስጥ 20 ሚሊዮን ዜጎች ተሳታፊ እንደሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ወደ አምስት የሚጠጉ አገሮችም ተሳትፈዋል፡፡ ችግኞቹ ወደ 121 ሺሕ በሚሆኑ የችግኝ ጣቢያዎች እንደተመረቱ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡  

አራተኛውን የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ በጉለሌ ቦታኒክ ጋርደን ያስጀመሩ ሲሆን፣ ሁሉም ሚኒስትሮች፣ የክልሎች ፕሬዚዳንቶች፣ የተለያዩ ተቋማት ሹማምንቶች፣ እንዲሁም አፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ሚስተር ሙሳፋኪ፣ የተለያዩ አገሮች አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች በችግኝ ተከላው ተሳትፈዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...