አይዞህ! ‹‹አንድ ቀን›› ይሳካል!!
ሁሉም ለበጎ ነው ነገር ሁሉ ያልፋል
ዛሬ ያልተቃናው ያልሆነበት ምስጢር
እንዲህ ነው… እንዲያ ነው…
እያልኩኝ ለ‹‹ራሴ›› ቀን በቀን ስነግር
እራሴን ሰደልል ምክንያት ስደረድር
በሰውኛ ቋንቋ ‹‹ራሴ›› አፋ’ውጥቶ
‹‹መቼ ነው ‘አንድ ቀን?’ መቼ ይሆን ከቶ?››
ብሎ ቢጠይቀኝ
ምላሹን ስላጣሁ ግራ ስለገባኝ
‹‹ነገ ነግርሃለሁ ዛሬን ብቻ ተወኝ››
ብዬ መለስኩለት
‹‹ራሴን›› ደግሜ መልሼ ሸወድኩት
አንተም እንደ ‹‹ራሴ›› ሰውኛ ከገባህ
እስኪ መልስ ካለህ ንገረኝ እራስህ
አንድ ቀን! መቼ ነህ?
- ዳንኤል ቢሰጥ እቴቴ ‹‹አፈር ብላ›› (2006)