Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ

የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ

ቀን:

የ2014 ዓ.ም. የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ  በቅዱስ ጊዮርጊስ የበላይነት ተጠናቋል። ፈረሰኞቹ በ30ኛው ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታቸውን ሰኔ 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ጋር በባህር ዳር ስታዲየም አድርገው 4ለ0 አሸንፈዋል። ፕሪሚየር ሊጉ በአዲስ መልክ በ1990 ከተጀመረ ወዲህ ይኸኛው ዋንጫ ያነሱበት ድላቸው ለ15ኛ ጊዜ ሆኗል። ለቅዱስ ጊዮርጊስ ኢስማኤል ኦሮ አጎሮ በ17ኛው ደቂቃ እና በ54ኛው ደቂቃ በጨዋታና በፍፁም ቅጣት ምት እንዲሁም አማኑኤል ገብረሚካኤል በ89ኛው እና በ93ኛው ደቂቃዎች ላይ ግቦቹን አስቆጥረዋል። በተመሳሳይ ጊዜ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሜዳ በተካሄደው ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ የዓምናውን ሻምፒዮን ፋሲል ከነማን 3ለ2 በሆነ ውጤት ረትቷል። ድሬዳዋ በማሸነፉ ከመውረድ ሲተርፍ፣ በጊዮርጊስ የተሸነፈው አዲስ አበባ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱን አረጋግጧል። ሌሎቹ አስቀድመው መውረዳቸውን ያረጋገጡት ሰበታ ከተማና ጅማ አባ ጅፋር ናቸው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሻምፒዮን የሆነው በ65 ነጥብ ሲሆን በአራት ነጥብ የተበለጠው ፋሲል ከነማ  በሁለተኛነት ያጠናቀቀው በ61 ነጥብ ነው።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...