- Advertisement -

ለትግራይ የተገዛው ነዳጅ ከጅቡቲ መግባት ጀመረ

  • ድርድርን በሚመለከት የአሜሪካ መንግስት አቋም እንደማይዝ ተገለጸ
  • በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች 488 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ተደረገ

    መንግስት በወር ሁለት ሚሊዮን ሊትር ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል እንዲያስገባ የተፈቀደለት  የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤድ)፣ ወደ ክልሉ ለመላክ የገዛውን ነዳጅ የጫኑ ተሸከርካሪዎች ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ መሆናቸው ተገለጸ፡፡  

    የኢትዮጵያ መንግስት ዩኤስኤድ በወር ሁለት ሚሊዮን ሊትር ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል እንዲያስገባ የፈቀደው ባለፈው ወር ሲሆን ድርጅቱ ነዳጁን የሚያስገባው ከታክስ ነጻ መሆኑን ገልጿል፡፡

    ድርጅቱ የገዛውን ነዳጅ የጫኑ የመጀመሪያዎቹ ተሽከርካሪዎች ትናንት ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓም ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን አስታውቀዋል፡፡ ትሬሲ አክለውም፣ መኪኖቹ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ይሄዳሉ የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

    ጉዳይ አስፈጻሚዋ ይሄንን የገለጹት ዛሬ ሐምሌ 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ዩኤስኤድ በኢትዮጵያ በድርቅ ለተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎች ድጋፍ የሚውል የ488 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ ባደረገበት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡

    ድርጅቱ ዛሬ ይፋ ባደረገው 488 ሚሊዮን ዶላር ድርቅ ባለባቸው አከባቢዎች የሚገኙ ከአራት ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለመድረስ አቅዷል፡፡ ይሁንና በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ወስጥ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት 8.1 ሚሊዮን ሰዎች እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ድርጅቱ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ አስታውቋል፡፡

    በመግለጫው ላይ፣ የፌደራል መንግስትና ህወሃት ሊያደርጉ ስላሰቡት ድርድር የአሜሪካ መንግስት አቋም ምን እንደሆነና የአሜሪካ መንግስት በማን ጥላ ስር የሚደረግ ድርድርን እንደሚደግፍ ለአምባሳደር ትሬሲ ጥያቄ ቀርቧል፡፡  

    - Advertisement -

    ጉዳይ አስፈጻሚዋ የአሜሪካ መንግስት ሁለቱ አካላት ወደ ድርድር ለመግባት መወሰናቸውን በመልካም እንደሚያየውና ለአፍሪካ ህብረትም ሙሉ ድጋፍ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ድርድሩ እንዴት፣ መቼና በምን አይነት ሁኔታ ይካሄድ የሚለው ላይ አቋም እንደማይዝ አስታውቀዋል፡፡ ትሬሲ ይሄንን ሲያስረዱም፣ “ንግግሩ እንዴት ይሂድና መቼ ይደረግ የሚሉ ዝርዝሮች የተደራዳሪዎቹ ጉዳይ ነው፡፡ እኛ ያ እንዴት መከናወን አለበት፣ ማን ምን ያድርግ የሚለው ላይ አቋም አንይዝም” በማለት ተናግረዋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ይፋ መደረጉ ተሰማ

ከመንግሥት የመገናኛ ብዙኃን በተጨማሪ የተወሰኑ የውጭ ሚዲያዎችና ለመንግሥት ቅርብ የሆኑ የአገር ውስጥ የግል ሚዲያዎች ብቻ እንዲዘግቡት በተደረገው፣ የኢትዮጵያን የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ማስጀመሪያ ሥነ...

በ1.5 ቢሊዮን ብር ይገነባል የተባለው የመንገድ ፕሮጀክት ሁለት የመንግሥት ተቋማትን እያወዛገበ ነው

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽንና አማካሪው የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከአራት ዓመታት በፊት በ1.5 ቢሊዮን ብር ለመገንባት ውል በተገባበት 65.1 ኪሎ ሜትር ርዝመት...

በበዓላትና በስብሰባዎች ሰበብ ሰዎችን በግዳጅ ከጎዳና አፍሶ መጋዘኖች ውስጥ ማቆየት እንዲቆም ኢሰመኮ ጠየቀ

ከአደባባይ በዓላትና ከዓለም አቀፋዊና አኅጉራዊ ስብሰባዎች ጋር በተያያዘ ውሎና አዳራቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ሰዎችን በግዳጅ ወደ ማቆያ ማዕከል ማስገባትና ማቆየት ሊቆም ይገባል ሲል፣ የኢትዮጵያ...

ልሂቅ የምጣኔ ሀብት ባለሙያና ፖለቲከኛ በፍቃዱ ደግፌ (ዶ/ር) ሲታወሱ

የምጣኔ ሀብት (ኢኮኖሚክስ) ዕውቀትን እስከ ሦስተኛ ዲግሪ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል በከፍተኛ ደረጃ ያስተማሩ፣ ያማከሩ ነበሩ፡፡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የነበራቸው የአገልግሎት ቁርጠኝነት...

የጫካ ፕሮጀክት አንድ አካል የሆነ የ21 ቢሊዮን ብር መኖሪያ መንደር ሊገነባ ነው

የጫካ ፕሮጀክት አንድ አካል እንደሆነ የተነገረለት የመኖሪያ መንደር በ21 ቢሊዮን ብር መነሻ ካፒታል ሊገነባ መሆኑን ኦቪድ ሪል ስቴት አስታወቀ፡፡ ኦቪድ ሪል ስቴት ይህንን ያስታወቀው ጥር...

አገራዊ የፖለቲካ ለውጦችና የትግራይ የውስጥ ፖለቲካ ውዝግብ

በትግራይ ክልል የተፈጠረው የፖለቲካ ውዝግብ አልሰከነም፡፡ በየጊዜው አዲስ መልክና ገጽታ እየያዘ የቀጠለው የሕወሓት አመራሮች ውዝግብ በቀላሉ መቋጫ ሳያገኝ ቀጥሏል፡፡ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የትግራይ...

አዳዲስ ጽሁፎች

የቤተሰብ ኃላፊነት የተሸከሙ ሕፃናት

በመማሪያና በለጋ ዕድሜያቸው የቤተሰብ ኃላፊነት ተጭኖባቸው ከትምህርት ገበታ ርቀው የሚቀሩ ሕፃናት በርካታ ናቸው፡፡ በቤተሰብ መበተን፣ ከቀዬ በመፈናቀልና በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሕፃናትና ታዳጊዎች ሲለምኑ፣ ሶፍትና...

አሸናፊና ተሸናፊ የሌለበት ትንቅንቅ ማብቂያው መቼ ይሆን?

በናኦድ አባተ በአውሮፓውያን ዘንድ በስፋት የሚታወቀው “A House Divided Against Itself Cannot Stand.” (እርስ በርሱ የተከፋፈለ ቤት አይቆምም) አባባል ትልቅ መልዕክት አለው፡፡ ኢትዮጵያውያንም በታሪክ አጋጣሚ...

መንግሥት በነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ላይ ቆም ብሎ ሊያስብ ይገባል!

በአገር ደረጃ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ከሚጠይቁ ገቢ ምርቶች መካከል ነዳጅና የነዳጅ ውጤቶች በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ አገሪቱ ከምታገኘው አነስተኛ የወጪ ንግድ ገቢ ከግማሽ በላይ የሚሆነው...

ስለመነጋገር እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪያ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ይፋ መደረጉ ተሰማ

ከመንግሥት የመገናኛ ብዙኃን በተጨማሪ የተወሰኑ የውጭ ሚዲያዎችና ለመንግሥት ቅርብ የሆኑ የአገር ውስጥ የግል ሚዲያዎች ብቻ እንዲዘግቡት በተደረገው፣ የኢትዮጵያን የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ማስጀመሪያ ሥነ...

በ1.5 ቢሊዮን ብር ይገነባል የተባለው የመንገድ ፕሮጀክት ሁለት የመንግሥት ተቋማትን እያወዛገበ ነው

የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽንና አማካሪው የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከአራት ዓመታት በፊት በ1.5 ቢሊዮን ብር ለመገንባት ውል በተገባበት 65.1 ኪሎ ሜትር ርዝመት...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን