Friday, December 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ወዳጃቸው ከሆነ አንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ጋር ሻይ ቡና እያሉ በኬንያ ስለተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እየተጫወቱ ነው]

  • ኬንያ በዚህ ደረጃ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ታደርጋለች ብዬ አላሰብኩም ነበር ክቡር ሚኒስትር።
  • አዎ። ጥሩ ዝግጅት አድርገውበታል። ቢሆንም…
  • ቢሆንም ምን ክቡር ሚኒስትር? 
  • እባክህ ክቡር ሚኒስትር የምትለውን ነገር አቁም። ወዳጅ አይደለንም እንዴ?
  • እሱማ ልክ ነው። ለተቋሙ ክብር መስጠት ስላለብኝ ነው። 
  • ቢሆንም… አሁን ያለነው ከተቋሙ ውጪ ነው።
  • ይልቅ እሱን አርሳውና ያቋረጥነውን ጨዋታ ቀጥል። ቢሆንም ብለህ ነበር ያቋረጥነው። ምን ልትል ነበር?
  • እ… አዎ። የኬንያ ምርጫ ጥሩ እንደነበረ እያወራን ነበር።
  • ጥሩ ብቻ ክቡር ሚኒስትር ለቀጣናው ጭምር ተምሳሌት የሚባል ነው እንጂ?
  • አንተ ደግሞ በጣም አጋነንከው። በምንም መመዘኛ ከስድተኛው የእኛ ምርጫ ውድድር አይበልጥም። 
  • እኔ ግን በእኛ አገር የምርጫ ውድድር ተካሂዶ ያውቃል ለማለት እቸገራለሁ። ብቻችሁን አይደል እንዴ የተወዳደራችሁት? የእነሱ ግን …
  • የእነሱ በምን ከእኛ በምን ይለያል?
  • በተተኪው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳይቀር ስንት ጫና ሲደረግባቸው የነበሩት ግለሰብ ጫናውን ተቋቁመው ለማሸነፍ የቻሉት ጥሩ የምርጫ ሥርዓት ስለገነቡ እንጂ እንደ እኛ ቢሆን ውጤቱ ሌላ ነበር የሚሆነው። 
  • ለማንኛውም ዊሊያም ሩቶ ቀጣዩ የኬንያ ፕሬዚዳንት ሆነው በማሸነፋቸው እኛም ልዩ ደስታ ተሰምቶናል። 
  • የእናንተን ደስታ ምን ልዩ ያደርገዋል? 
  • ሰውዬው ምን እንደሆኑ አታውቅም እንዴ? 
  • ዊሊያም ሩቶ? 
  • እህሳ?
  • ምንድናቸው? 
  • የእኛው ብሔር እኮ ናቸው? 
  • አይ እናንተ… መቼም አትለወጡም በቃ? 
  • እንዴት?
  • ምን ልትሉ እንደሆነ ገብቶኛል?
  • ምን እንላለን? 
  • ሩቶ ኬኛ!

[ክቡር ሚኒስትሩ በስንዴ ምርት ራስን የመቻል ጥረትን በተመለከተ የተላለፈውን የምሽት ዜና ከባለቤታቸው ጋር ተመልክተው በዚህ ዙሪያ እየተጨዋወቱ ነው]

  • ትልቅ ስኬት እንደምናስመዘግብ ጥርጥር የለውም።
  • በምን ጉዳይ?
  • በስንዴ ምርት ነዋ? ዜናውን እየተከታተልሽ መስሎኝ ነበር እኮ? እንደ ቀልድ የተቆጠረው ጥረታችን ዛሬ የት እንደደረሰ አላየሽም?
  • እሱስ ተመልክቻለሁ። ጥሩ ጅምር ይመስላል ግን…
  • ግን ምን? 
  • አሜሪካ ግን ይህንን ጥረት ለማቆሸሽ ይመስላል፡፡
  • እንዴት?
  • እናንተ ዘንድ ምንም ዓይነት የስንዴ ምርት ከውጭ አልሸመትንም እያላችሁ አይደል?
  • ትክክል ነው! እንደውም ከመጪው ዓመት ጀምሮ ወደ ጎረቤት አገሮች ኤክስፖርት ማድረግ እንጀምራለን።
  • እናንተ ዘንድሮ ስንዴ ከውጭ አናስገባም ብትሉም አሜሪካ ግን ለኢትዮጵያ የተገዛው ስንዴ ወደ አገሪቱ እየተጓጓዘ ነው የሚል መረጃ እያሠራጨች ነው። 
  • መቼ ነው ይህንን መረጃ ያሠራጨችው?
  • ጠቅላዩ በስንዴ ማሳዎች ጉብኝት እያደረጉ በነበረበት ቀን መሰለኝ፡፡ አዎ በዚያው ቀን ነው።
  • ከዚህ ሴራ ጀርባ ማን እንዳለ ግልጽ ነው።
  • ሴራ? ማነው ያለው?
  • ጁንታው ነዋ!
  • መረጃውን ያሠራጨችው እኮ አሜሪካ ነች?
  • ያው ናቸው! ለማንኛውም …
  • እህ… ለማንኛውም? ስንዴውን አንቀበልም እንዳትለኝ ብቻ?!
  • ለምን አንቀበልም …እንቀበላለን እንጂ፡፡ 
  • እኮ…
  • ግን አንድ ነገር መታወቅ አለበት።
  • ምን?
  • እኛ ያዘዝነው ስንዴ የለም! ከመጣ ግን አንቀበልም አንልም። 
  • ዋናው እሱ ነው። ስንዴውን ተቀብሎ የተጀመረውን በስንዴ ራስን የመቻል ጥረት መቀጠል። 
  • ትክልል ነው። አየሽ አይደል ምን ያህል ማሳ በበጋ ስንዴ እንደተሸፈነ? 
  • ምን ያህል ተሸፈነ? 
  • በሶማሌ ክልል ብቻ 127 ሺሕ ሔክታር በስንዴ እየለማ ነው። 
  • ስንት ማለት ነው 127 ሺሕ ሔክታር? ብዙ ነው እንዴ? 
  • አንቺና ቁጥር መቼም አትዋደዱም። 
  • ምን ያህል እንደሆነ ለምን አታስረዳኝም?
  • ቆይ… እንዴት ላስረዳሽ? አዎ… ስንት መሰለሽ…?
  • እህ… ስንት ነው?
  • የአዲስ አበባ ከተማን በሁለት እጥፍ የሚበልጥ የስነዴ ማሳ እንደ ማለት ነው። 
  • አትቀልድ?!
  • የምሬን ነው! 
  • በአዲሱ ነው፣ በድሮው ስፋቷ?
  • አዲሱ ደግሞ ምንድነው? 
  • የከተማዋ አከላለል ማለቴ ነው። 
  • ቁምነገር እያወራን ለምን ትቀልጃለሽ?
  • ቀልዴን አይደለም? እንደውም ካነሳነው አይቀር ልጠይቅህ?
  • ምን?
  • አሁን እኛ የምንኖርበት ቤት አዲስ አበባ ውስጥ ነው? 
  • ዛሬ ምን ሆነሻል? ስለ በጋ ስንዴ ስኬታችን እንዲወራ አልፈለግሽም? 
  • ኧረ እንደዚያ አይደለም። 
  • ታዲያ ምን እየሆንሽ ነው? 
  • የበጋ ስንዴው ስኬትማ በሌሎች ምርቶችም ቢደገም ጥሩ ነው። 
  • እሱማ አይቀርም። ይደገማል!
  • በተለይ ነዳጅ ላይ ብትረባረቡ ጥሩ ነው። 
  • ነዳጅ? 
  • አዎ።
  • የምን ነዳጅ?
  • የበጋ ነዳጅ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...

ሀብቱንና ትርፉን እያሳደገ የቀጠለው አዋሽ ባንክ

አዋሽ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዋና መሥሪያ ቤት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ ቢያብራሩት? ከአራት ዓመት በፊት በኦጋዴን አካባቢ ነዳጅ መገኘቱን ለሕዝብ በቴሌቪዥን አብስሮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...

[ጉባዔው በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ክቡር ሚኒስትሩን ለመጠየቅና ምላሽና ማብራሪያቸውን ለማድመጥ ተሰብስቧል። የጉባዔው አባላትም ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎቻቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር፣ ይህ ጉባዔ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት በመካከላችን ስለተገኙ አመሰግናለሁ። ክቡር ሚኒስትር፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የብሪክስ አባል እንድትሆን የሰጡት በሳል አመራር የሚደነቅ ነው። አገራችን...