Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍር‹‹ደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያና የሱዳን የድንበር ውዝግብ ለመፍታት የሚያስችል ውይይት ለማዘጋጀት ፈቃደኛ ናት››

‹‹ደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያና የሱዳን የድንበር ውዝግብ ለመፍታት የሚያስችል ውይይት ለማዘጋጀት ፈቃደኛ ናት››

ቀን:

የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ብሔራዊ የደኅንነት አማካሪ ቱት ጋትሉክ ሚናሜ፣ ሰሞኑን በሱዳን በነበራቸው ጉብኝት ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፡፡ የደኅንነት አማካሪው ከሱዳን ጊዜያዊ ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀመንበር ጄኔራል አብዱልፈታህ አል ቡርሃን ጋር በሁለቱ አገሮች የፖለቲካና የድንበር ጉዳዮች ላይ በተወያዩበት ወቅት፣ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ከኢትዮጵያና ከሱዳን መሪዎች ጋር የሦስትዮሽ ውይይት የሚደረግበት ስብሰባ በማዘጋጀት የድንበር ውዝግቡን ለመፍታት ዕቅድ እንዳላቸው እንደ ነገሯቸው ዢኑዋ ከካርቱም ዘግቧል፡፡ ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሳ ገብታ ሰፋ ያለ መሬት በወረራ በመያዟ ምክንያት፣ በሁለቱ አገሮች መካከል መቃቃር መፈጠሩ ይታወሳል፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ችግሩ በዲፕሎማሲ ተፈቶ የሁለቱ አገሮች ወዳጅነት ወደ ነበረበት እንዲመለስ በተደጋጋሚ ማስታወቋ አይዘነጋም፡፡ በምሥሉ ላይ የሚታዩት የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ናቸው፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...