Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍር‹‹የአሜሪካና የቻይና ፍጥጫ የዓለምን ኢኮኖሚ ያዘቅጠዋል››

‹‹የአሜሪካና የቻይና ፍጥጫ የዓለምን ኢኮኖሚ ያዘቅጠዋል››

ቀን:

የዬል ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ መምህርና የአሜሪካ ፌዴራል ሪዘርቭ የቀድሞ ኢኮኖሚስት ስቴፈን ሮች፣ ለሲኤንቢሲ ቴሌቪዥን ጣቢያ ‹‹ፋስት መኒ›› የሰኞ ምሽት ፕሮግራም ካደረገላቸው ቃለ ምልልስ የተወሰደ፡፡ አሜሪካና ቻይና ‹‹ቀዝቃዛው ጦርነት›› ላይ ናቸው ያሉት አንጋፋው ኢኮኖሚስት፣ የሁለቱ አገሮች ፍጥጫ የዓለምን ኢኮኖሚ እንደሚያዘቅጠው አትጠራጠሩ ብለዋል፡፡ ባለፉት አምስት ዓመታት ሁለቱ አገሮች ከንግድ ጦርነት እስከ ቴክኖሎጂ ጦርነት አድርገዋል፡፡ አሁን ደግሞ ወደ ቀዝቃዛው ጦርነት ውስጥ በመግባት ተፋጠዋል ብለዋል፡፡ አሜሪካ የኢኮኖሚ ዝቅጠቱ እንዳያጋጥማት ተዓምር ያስፈልጋታል ያሉት ሮች፣ ቻይናም ብትሆን በኮቪድ ዜሮ ፖሊሲ፣ በምርቶች አቅርቦት ሰንሰለት መናጋትና ከምዕራባውያን ጋር በፈጠረችው ቅራኔ ምክንያት የችግሩ ሰለባ ትሆናለች ሲሉ ተንብየዋል፡፡ አሜሪካ በሥራ አጥነትና እያደር በሚያሻቅበው የዋጋ ግሽበት ሳቢያ የኢኮኖሚ ዝቅጠቱ ያስፈራታል ሲሉም አክለዋል፡፡

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...