Wednesday, September 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትቅዱስ ጊዮርጊስ ከሱዳኑ አል ሒላል ጋር ዛሬ በአዲሱ ዓመት መባቻ ይጫወታል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሱዳኑ አል ሒላል ጋር ዛሬ በአዲሱ ዓመት መባቻ ይጫወታል

ቀን:

በአፍሪካ የክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግ ኢትዮጵያን የሚወክለው አንጋፋው ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬ እሑድ መስከረም 1 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲሱ ዓመት መባቻ ከሱዳኑ አል ሒላል ጋር በባህር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

 አል ሒላል ባለፈው ሳምንት ከፀጥታ ሥጋት ጋር በተገናኘ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ጨዋታው በገለልተኛ አገር እንዲሆን ጠይቆ እንደነበረ ይታወሳል፡፡

ብዙ ጊዜ የውጭ ዜግነት ባላቸው አሠልጣኞች በመሠልጠን የሚታወቀው  ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ከዓመታት በኋላ በአገር ውስጥ አሠልጣኞች ያውም በቀድሞው የክለቡ ተጫዋች ዘሪሁን ሸንገታ እየተመራ ነው ጨዋታውን የሚያደርገው፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒዮንስ ሊግም ሆነ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ላይ ካፍ የውድድር ቅርፁን (ፎርማት) በአዲስ መልክ ከቀየረ በኋላ፣ በመድረኩ ውጤታማ ጉዞ በማድረግ ከአገሪቱ ክለቦች የመጀመሪያ ያደርገዋል፡፡ የውድድር ዓይነቱ ከመቀየሩ በፊት ግን ኢትዮጵያ መድን በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ጥሩ ደረጃ የደረሰበት አጋጣሚ እንደነበር አይዘነጋም፡፡

የዓምናው አሸናፊ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ለዚህ ጨዋታ ይረዳው ዘንድ ከቀናት በፊት ቢሾፍቱ (ደብረ ዘይት) በሚገኘው የይድነቃቸው ተሰማ አካዴሚ፣ ከሌላው የሱዳን ክለብ ከሆነው አልሜሪክ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ አድርጎ 3 ለ 1 ማሸነፉ ይታወሳል፡፡ የሱዳኑ አልሜሪክ ቀደም ብሎ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

ቀደም ሲል የባህር ዳሩ ጨዋታ በገለልተኛ አገር ሜዳ እንዲሆንለት ለካፍ ጥያቄ ያቀረበው የሱዳኑ አል ሒላል፣ ጥያቄው ተቀባይነት አለማግኘቱን ካወቀ በኋላ አዲስ አበባ የገባው ሐሙስ ጳጉሜን 3 ቀን 2014 ዓ.ም. ነው፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...