Saturday, December 9, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየሦስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ባለድሉ አምበል ሉቺያኖ ቫሳሎ (1927-2015)

የሦስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ባለድሉ አምበል ሉቺያኖ ቫሳሎ (1927-2015)

ቀን:

የአፍረካ እግር ኳስ ዋንጫ ሲታወስ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ስማቸው ቀድሞ ከሚታወሱ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ባለውለተኞች መካከል ስሙ በቀዳሚነት ይጠቀሳል፡፡ የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋችና አሠልጣኝ እንዲሁም የሦስተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ባለድሉ ብሔራዊ ቡድን አምበል ሉቺያኖ ቫሳሎ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

ትውልዱ በኤርትራ በ1927 ዓ.ም. እንደሆነ የሚነገርለት ሉቺያኖ ቫሳሎ፣ እሱና ወንድሙ ኢታሎ ቫሳሎ የዚያ ትውልድ አካል ከመሆናቸው ባሻገር፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ሁሌም ከፊት የሚያስቀድማቸው በታሪካዊ ውለታቸው አይረሴ ስለመሆናቸው ጭምር ብዙዎች ይመሰክሩላቸዋል፡፡

ሕልፈቱ እስከተሰማበት ጊዜ ድረስ በጣሊያኗ ሊዶ ከተማ የኖረው ሉቺያኖ ቫሳሎ፣ በእግር ኳስ ሕይወቱ ቀድሞ ድሬዳዋ ጥጥ ማኅበር (ወደ ኋላ ላይ ድሬዳዋ ጨርቃ ጨርቅ) እንዲሁም ለቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ በመጫወት ይታወቃል፡፡

በዘመኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች ሆኖ ባደረጋቸው በተለያዩ የአፍሪካ ዋንጫዎች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል፣ ከቡድኑ ጋር ታሪካዊ ተብሎ እስካሁን የሚጠቀሰውን ሦስተኛውን የአፍሪካ ዋንጫ ለኢትዮጵያ ከፍ ያደረገ ድንቅ እግር ኳሰኛ እንደነበርም በግለ ታሪኩ የቀረቡ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡

በ1954 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በተደረገው የ3ኛ አፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ ግብፅን 4 ለ2 ኢትዮጵያ ስታሸንፍ ወሳኝ ግብ ያስቆጠረው ሉቺያኖ ቫሳሎ፣ እግር ኳስ እንዲህ እንደ አሁኑ ባልዘመነበት በዚያን ዘመን ከተጨዋችነት ሕይወቱ በተጨማሪ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ቡድን በማሠልጠን ታሪክ የሚያስታውሰው ድንቅ እግር ኳሰኛ ነበር፡፡

ታላቁ የእግር ኳስ ሰው ሉቺያኖ ቫሳሎ ባሳለፍነው ሳምንት በ87 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ተከትሎ ብዙዎች ሐዘናቸውን እየገለጹለት ይገኛል፡፡ የሉቺያኖ ቫሳሎ ሥርዓተ ቀብር በሚኖርበት ጣሊያን ሊዶ ከተማ ቅድስት ሞኒካ ቤተ ክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ተፈጽሟል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...