የማዕድንና ሚኒስቴር በሶማሌ ክልል የተገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ አልምቶ ኤክስፖርት ለማድረግና ለተጨማሪ የፔትሮሊየም (የነዳጅ ዘይት) ፍለጋና ልማት፣ በዚሁ አካባቢ ለማካሄድ ፈቃድ ላገኘው የቻይናው ፖሊጂሲኤል ኩባንያ የሰጠውን ውል አቋረጠ።
የማዕድን ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ(ኢንጂነር ) እንዳስታወቁት ፣ መንግስት ኩባንያው ያለውን ዓቅም ተጠቅሞ እንዲሰራ ለማድረግ ጥረት ቢያደርግም ኩባንያው የሚጠበቅበትን የማልማት፣ የፋይናንስና ቴክኖሎጂ አቅም ማሳካት ስላልቻለ ከዛሬ መስከረም 11 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ውሉ ተቋርጧል ብለዋል። በቀጣይ ኩባንያው መንግስት እንዲያሟላ የጠየቀውን ቅድመ ሁኔታዎች የሚያሟላ ከሆነ ዳግም የሚስተናገድበት ዕድል እንዳለ ሚንስትሩ አክለዋል።