Tuesday, November 28, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ እንኳን ደስ አለዎት እያለ ወደ ቢሯቸው ገብቶ በጨዋታና መረጃ በመፈለግ መካከል ያለ ጥረት እያደረገ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር እጅግ የሚያስደስት ነገር ነው። እንኳን ደስ አለዎት፡፡
  • ምኑ? ምን ተገኘ?
  • ባለፈው የነገሩኝ ስልት በጣም ውጤታማ ነው። 
  • የቱ ስልት? 
  • እንዴ ክቡር ሚኒስትር ባለፈው ያጫወቱኝ ነዋ? ለማንኛውም በኃይል ከያዙት አካባቢ እግሬ አውጪኝ ብለዋል።
  • እውነት፡፡
  • አዎ። አልሰሙም እንዴ?
  • እኔ ምንም የሰማሁት ነገር የለም። 
  • የምርዎትን ነው ክቡር ሚኒስትር? 
  • አልሰማሁም ስልህ? 
  • የካቢኔ አባል ሆነው ምንም ካልሰሙ ተግባራዊ የሆነው ስልት በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚፈጸም ነው ያሰኛል።
  • የቱ ስልት? 
  • ባለፈው የነገሩኝን የውጊያ ስልት ማለቴ ነው። 
  • የውጊያ ስልት? እኔ ነኝ የነገርኩህ?
  • አዎ!
  • ምን ብዬ?
  • ምታ በዝምታ!
  • በጭራሽ አላስታውስም… እርግጠኛ ነህ እኔ ነኝ የነገረኩህ? 
  • አሃ …ገባኝ ገባኝ!
  • ምን?
  • በዘዴ እየነገሩኝ እንደሆነ ገባኝ። 
  • በዘዴ የገባህ ምንድነው? 
  • ማስተካከያ እንደተደረገበት።
  • ምኑ?
  • ምታ በዝምታ። 
  • ምን ተባለ?
  • ምታ በዝምታ ጠላት እስኪምታታ፡፡
  • ኦሆሆ… አንተ መቼም…
  • እውነቴን ነው እንደዚያ እኮ ነው ያደረጋቸው?
  • ምኑ?
  • ምቱ!
  • እንዴት? 
  • መጀመሪያ ለቀን ነው የወጣነው አሉ።
  • እሺ፡፡
  • ቀጥሎ ደግሞ ተሸንፈን አይደለም ስትራቴጂክ የቦታ ለውጥ ነው አሉ።
  • ማን ተሸንፋችሁ ነው አለ? 
  • እሱን እኮ ነው የምልዎት፡፡
  • እሺ፡፡ 
  • ቀጥሎ ደግሞ መንግሥት ራሱ መግለጫ አለመስጠቱ የሚያረጋግጠው ተሸንፈን አለመውጣታችን ነው አሉ።
  • መንግሥት አሁንም በዝምታው ሲቀጥል ደግሞ ምን አሉ መሰሎት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እህ…
  • እንገናኛለን፡፡
  • ኪኪኪ… ወይ አንተ!
  • በዚህ ከቀጠሉ ወደፊት ምን የሚሉ ይመስልዎታል? 
  • እ…?
  • እጅ በእጅ!
  • እጅ በእጅ ምን?
  • እጅ በእጅ ይዋጣልን!

[ክቡሩ ሚኒስትሩ ከዓብይ የሰላም ኮሚቴው ጋር ድርድሩን የተመለከተ ሪፖርት ተቀብለው ተጨማሪ መረጃ እየጠየቁ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በእኛ በኩል ማድረግ የሚገባንን ዝግጅት አድርገናል ነገር ግን …
  • ነገር ግን ምን?
  • ክቡር ሚኒስትር ሌላኛው ተደራዳሪ አቋሙን የቀየረ ይመስላል? 
  • እንዴት? ምን ተፈጠረ? 
  • እኛን ቅርቃር ውስጥ ለማስገባት አልሞ የዘመን መለወጫ ቀን ላይ በአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነት ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን አሳውቆ አልነበር?
  • አዎ። 
  • የአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነትን መቀበል ብቻ ሳይሆን ያለ ቅድመ ሁኔታ ለመደራደርም ዝግጁ መሆኑን ለማሳየት ቅድመ ሁኔታ የሌለው ጥሪ ነበር ያቀረበው። 
  • አዎ። አስታውሳለሁ፡፡
  • አሁን ወደ ድርድር ለመግባት ጥረቶች ሲጀመሩ ወደ ቀደመ አቋሙ ተመልሷል።
  • ወደ ቀደመ አቋሙ ማለት? 
  • የአፍሪካ ኅብረት አደራዳሪነትን ብቀበልም ዋና አደራዳሪውን አልቀበልም እያሉ ነው። 
  • እንደዚያ አሉ?
  • እሱ ብቻ ሳይሆን ቀደም ሲል ያስቀመጣቸውን ሁሉንም ቅድመ ሁኔታዎች ዳግም በቅድመ ሁኔታነት እያቀረበ ነው።
  • እርግጠኛ ነህ? 
  • አዎ። ተደራዳሪ ተብለው የተመደቡት ሰዎዬ ናቸው በይፋ የተናገሩት።
  • እንደዚያ ከሆነ እኚህን ተደራዳሪ መንግሥት እንደማንቀበል ለአደራዳሪዎቹ እሳውቁ፡፡
  • እንዴት? ለምን ብለው ቢጠይቁንስ? 
  • በመጀመሪያ ሕጋዊ ዕወቅና ያለው የክልል መንግሥት ባለመኖሩ ድርድሩን የምናደርገው ከክልሉ ፓርቲ ጋር እንደሆነ አሳውቋቸው። 
  • ጥሩ። ከዚያ በኋላስ?
  • ሰውዬው የክልሉ ፓርቲ አባል እንዳልሆኑ ጠቅሳችሁ እንደማንቀበል አሳውቁ። 
  • እሺ። ጥሩ መላ ነው። 
  • ሌላ የገጠማችሁ ችግር አለ?
  • ትልቅ ችግር አለ ክቡር ሚኒስትር። 
  • ምንድነው? 
  • በድርድሩ መሳተፍና ሚና እንዲኖራቸው የሚፈልጉ አገሮች ቁጥር እየጨመረ ነው።
  • የትኞቹ አገሮች ናቸው። 
  • የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አለ። አሜሪካና የአውሮፓ ኅብረትም መሳተፍ አለብን እያሉ ነው።
  • የተባበሩት መንግሥታት አይበቃም እንዴ? 
  • እኛ የሌለንበት ድርድር አይታሰብም እያሉ ነው። እነሱን ተከትሎ ደግሞ ሌሎች አገሮችም ጥያቄ አቅርበዋል።
  • የትኞቹ አገሮች?
  • ሩሲያ፣ ቻይናና የዓረብ አገሮች ናቸው። በዚህም ምክንያት ማን ታዛቢ መሆን አለበት የሚለው ላይ ስምምነት ጠፍቷል።
  • ሌላ ድርድር ገጥሞናል ማለት ነዋ?
  • አዎ።
  • ጥሩ ነው፡፡
  • እንዴት?
  • እነሱ እስኪስማሙ እኛ ፈትተን እንጠብቃቸዋለን።
  • ምኑን ፈትተን?
  • የውስጥ ችግራችንን!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ ሲኒመር ትሬዲንግ...

የባህር በር በቀጣናዊ ተዛምዶ ውስጥ

በበቀለ ሹሜ መግቢያ በ2010 ዓ.ም. መጋቢት ማለቂያን ይዞ ዓብይ አህመድ በጠቅላይ...

ሥጋት ያስቀራል ተብሎ የሚታሰበው የጫኝና አውራጅ መመርያ

በአዲስ አበባ ከተማ በሕገወጥ መልኩ በመደራጀት ማኅበረሰቡ ላይ እንግልትና...

ማወቅ ወይስ አለማወቅ – ድፍረት ወይስ ፍርኃት?

በአሰፋ አደፍርስ ወገኖቼ ፈርተንም ደፍረንም የትም አንደርስምና ለአገራችን ሰላምና ክብር...

ከድህነት ወለል በታች ከሆኑት አፍሪካዊያን ውስጥ 36 በመቶው በኢትዮጵያ ናይጄሪያና ኮንጎ እንደሚገኙ ተጠቆመ

‹‹ለሺሕ ዓመት በድህነት ውስጥ የነበረች አገርን በአሥር ዓመት ልንቀይር...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...

[ጉባዔው በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ክቡር ሚኒስትሩን ለመጠየቅና ምላሽና ማብራሪያቸውን ለማድመጥ ተሰብስቧል። የጉባዔው አባላትም ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎቻቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር፣ ይህ ጉባዔ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት በመካከላችን ስለተገኙ አመሰግናለሁ። ክቡር ሚኒስትር፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የብሪክስ አባል እንድትሆን የሰጡት በሳል አመራር የሚደነቅ ነው። አገራችን...

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሚመሩት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ተጠሪ የሆነው ተቋም የዋና ሥራ አስኪያጅና ለእሳቸውም የቅርብ ወዳጅ የሆኑትን ግለሰብ ቢሯቸው አስጠርተው ከበላይ አካል እንዲሰጡ የታዘዙትን ደብዳቤ...

የምን ደብዳቤ ነው ክቡር ሚኒስትር? ከበላይ አካል የተወሰነ ነው። የምን ውሳኔ ነው? እስኪ ተመልከተው። እሺ... አዋከብኩዎት አይደል .... ምን? ምንድነው ክቡር ሚኒስትር? ከሥራ መሰናበትዎን ስለማሳወቅ ነው እኮ የሚለው፡፡ እኔም...