- Advertisement -

የ ሳ ም ን ቱ ገ ጠ መ ኝ

ከድሮ ጀምሮ ‘አንድ ሰው ጥፋተኛ መሆኑ ካልተረጋገጠ በስተቀር ንፁህ ነው’ በሚለው አባባል ለመመራት እጥራለሁ፡፡ በተመሳሳይ ተቃራኒ ማስረጃ ካልቀረበ በስተቀር አአራችን አሁን ባለችበት ዘመን በቋንቋ እንለያይ ይሆናል እንጂ ሁላችንም እኩል ኢትዮጵያዊያን ነን፡፡  ሁላችንም አገራችንን እኩል እንወዳለን፡፡ ለልማቷም እኩል እንጥራለን  በሚለውም  አምናለሁ፡፡ አንዳንዴ ግን ግራ የሚያጋባ ነገር ያጋጥመኛል፡፡ ታላቅ ወንድሜ የጡረታ ዘመኑን ከባለቤቱ ጋር ለማሳለፍ አንድ ከአዲስ አበባ ጋር የሚዋሰንና በኦሮሚያ ክልል የሚገኝ መለስተኛ ከተማ ውስጥ ቤት ገዝቶ ይገባል፡፡ በእቅዱም መሠረት ግማሽ ዓመት በዚሁ ከተማ፣ ግማሹን ዓመት ደግሞ በውጭ አገር ከሚኖሩት ልጆቹና የልጅ ልጆቹ ጋር ለመኖር ያቅድና የጡረታ ዘመኑን ሁለት ቦታ መኖር ይጀምራል፡፡

ታዲያ በቅርቡ እሱና ባለቤቱ ካሉበት ውጭ አገር ደውለው የቤታቸውን የቦታ ግብርና ኪራይ እንድከፍልላቸው ይጠይቁኛል፡፡ እኔም ውክልናዬንና አስፈላጊ ሰነዶችን ይዤ ግብርና ኪራይ ለመክፈል ወደ ከተማው የመሬት ልማትና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ሄድኩ፡፡ ከትንሽ ውጣ ውረድ በኋላ የሚመለከተውን ግለሰብ አገኘሁና ለወንድሜ የቦታ ግብርና ኪራይ ለመክፍል እንደመጣሁ አስረዳሁት፡፡ እሱም የውክልና ወረቀትህን አሳየኝ አለኝ፡፡ እኔም በጥንቃቄ የያዝኩትን የውክልና ወረቀት ከቦርሳዬ አውጥቼ አሳየሁት፡፡ እሱም ይህ በአማርኛ ስለሆነ ወደ ኦሮምኛ አስተርጉመህ አምጣ አለኝ፡፡ እኔም እሺ ብዬ አስተርጉሜ አመጣሁ፡፡

በመቀጠል የመታወቂያ ደብተሬን እንዳሳየው ጠየቀኝ፡፡ የመታወቂያ ደብተሬን ከኪሴ አውጥቼ አሳየሁት፡፡ ይህም ወደ ኦሮምኛ መተረጎም አለበት አለኝ፡፡ እኔም መታወቂያው ላይ ያለው መረጃ በአማርኛም በእንግሊዝኛም ስለሆነ መረጃውን ከአማርኛው መውሰድ ካልፈለገ ከእንግሊዝኛው ሊያገኘው እንደሚችል ላስረዳው ሞከርኩ፡፡ አሁንም አይሆንም ሂድና አስተርጉመህ አምጣ አለኝ፡፡ ምንም ምርጫ ስላልነበረኝ መታወቂያዬን ወደ ኦሮምኛ አስተርጉሜ አመጣሁ፡፡

ከዚያ የሚከፈለውን የቦታ ግብርና ኪራይ መጠን ነገረኝ፡፡ እኔም ጥሬ ገንዘብ በኪሴ ስለነበር ለመክፈል ስዘጋጅ በጥሬ ገንዘብ መክፈል እንደማይቻል ነገረኝ፡፡ እሺ ብዬ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሄጄ ሲፒኦ (CPO) አሠርቼ አመጣለሁ አልኩ፡፡ እሱም አይቻልም አለኝ፡፡ ታዲያ ምን ላድርግ አልኩት፡፡ ኦሮምያ ኅብረት ሥራ ባንክ የቁጠባ ሒሳብ አለህ ወይ ብሎ ጠየቀኝ፡፡ እኔም እንደሌለኝ ነገርኩት፡፡ በል እንግዲህ እዚያ ሂድና የቁጠባ ሒሳብ ክፈት፣ ከዚያ ቢያንስ የግብርና ኪራይ መጠን ያክል ገንዘብ አስገባና ተመልሰህ እኔጋ ና አለኝ፡፡ ትንሽ ግራ ቢገባኝም ምንም ምርጫ ስላልነበረኝ የተባልኩትን አደረኩ፡፡ ከዚያ ገንዘቡን የማስገባበትን ሒሳብ ቁጥር ሰጠኝና ግብሩና ኪራዩን ከፈልኩ፡፡ በነገራችን ላይ ይህንን ለማድረግ ወደ ከተማው አስተዳደር 12 ጊዜ ተመላልሻለሁ፡፡ ልብ በሉ፣ ይህ ሁሉ ምልልስ እባካችሁ ገንዘብ ልስጣችሁ ባልኩ ነው፡፡

እንግዲህ ይታያችሁ፡፡ እሺ ውክልናዬ በአማርኛ ስለነበረ አሁን ባለው አሠራር መሠረት ወደ ክልሉ ቋንቋ ይተርጎም፡፡ መታወቂያዬ ግን በእንግሊዝኛም ጭምር ስለነበር ቅንነት ቢኖር ኖሮ በግድ መተርጎም አልነበረበትም፡፡ ለእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ካልጠቀመ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መታወቂያው ላይ የገባው ለቄንጥ ነው? ከሁሉም የባሰው ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ሲፒኦ (CPO) አንቀበለም፣ በግድ ኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ሄደህ ሒሳብ መክፈት አለብህ የሚለው ነው፡፡ ልብ በሉ፡፡ አንድ የመንግሥት የሆነ አካል አንድን ተገልጋይ ዜጋ በአክሲዮን መልክ ለትርፍ በተቋቋመ ተቋም የባንክ ሒሳብ እንድከፍት እያስገደደኝ ነው ማለት ነው፡፡ ከዚህ በላይ ሙስና አለ? ያውም በግላጭ!! እንዲህ ዓይነት ርካሽ ዘዴ አንዳንድ ሰዎች ለጊዜው ተጠቃቅመውበት ይሆናል እንጂ ወደፊት ለባንኩም ቢሆን አያዋጣውም፡፡ መስተካከል አለበት፡፡

ይገባኛል፡፡ ይህ ችግር አሁን አገራችን ካለችበት ችግሮች ጋር ሲነፃፀር ኢምንት ሊመስል ይችላል፡፡ እኔም በችግር ላይ ችግር ለምን እጨምራለሁ በሚል ባላነሳው ይሻል ይሆናል፡፡ ነገር ግን እንደነዚህ ዓይነት ችግሮች አሁን በሚቻልበት ጊዜ በአጭሩ ካልተቀጩ የሚያመጡት መዘዝ ዛሬ ከሚያተረማምሰን የብሔር ፖለቲካ ትኩሳት ጋር ተደማምረው ከማንወጣበት አዙሪት ውስጥ ሊከቱን ይችላሉ፡፡ ስለዚህ የሚሰማኝ ሰው ካለ የአቅሜን ምክር ልለግስ፡፡

- Advertisement -

ምክር አንድ፡- ይህና ተመሳሳይ ችግሮች በቀላሉ ሊስተካከሉ ይችላሉ፡፡ የሚያስፈልገው በተለይ አገልግሎት ከሚሰጡ አካላት ትንሽ ቅንነት ነው፡፡ ቅንነት ለሰው ልጅ በመከባበር አብሮ ለመኖር ዋነኛው እሴት እንደመሆኑ መጠን በቀላሉ ሊገኝ እንደማይችል ይገባኛል፡፡ አንድ ሰው ቅን ለመሆን መጀመሪያ በራሱ የሚተማመን ሰው መሆን አለበት፡፡ ይህ ቀላል አይደለም፣ ብስለትን ይጠይቃል፡፡ ካልሆነ የሰው መንገላታት የማይስማው ሰው ለጊዜው ትልቅነት ተሰምቶት ሊሆን ይችላል እንጂ በሥራውም በኑሮውም ደስተኛ ሊሆን አይችልም፡፡ የኋላ ኋላ ተሸናፊው እሱ ነው፡፡ በአንፃሩ ቅን ለመሆን የሚጥር ሰው በማንኛውም መመዘኛ በኑሮውም በሥራውም ደስተኛ ነው፡፡ የኋላ ኋላ አሸናፊው እሱ ነው፡፡

ምክር ሁለት፡- ከላይ እንደጠቀስኩት ይህ ሁሉ ጣጣ ገንዘብ ልክፈል ባልኩ ነው፡፡ ከከተማው ነዋሪ በግብር መልክ የሚሰበስበው ገንዘብ የሚጠቅመው በመጀመሪያ ደረጃ የከተማዋን ነዋሪዎች መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ነዋሪው ውኃ፣ መንገድ፣ ክሊኒክ ትምህርት እንዲሠሩለት ይፈልግ የለ? የከተማው አስተዳዳሪዎች ይህ አይገባቸውም? ሥራቸውስ ይህ አይደለም? ስለእውነት ከሆነ ወንድሜ ሦስት መኝታ ቤት ላለውና 500 ካሬ ሜትር ላይ ላረፈ ዘመናዊ ቪላ የሚከፍለው የቦታ ግብርና ኪራይ በጣም ትንሽ ነው፡፡ አንድ ዘመዴ ሲነግረኝ የቦታ ግብርና ኪራይ ከሚከፍለው ገንዘብ ይልቅ ለግብር ተመን አገልግሎት የሚከፍለው ገንዘብ ይበልጣል! አሁን ይህ ምን ይባላል?

እኔ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነኝ ወንድሜ ለዚህ ቤት አሁን ከሚከፍለው ግብርና ኪራይ ሁለት ሦስት እጥፍ ምንም ቅር ሳይለው ለመክፈል ፈቃደኛ ይሆናል፡፡ አቅሙም አለው፡፡ ይህ ለሌሎችም ተመሳሳይ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ፡፡ ምክንያቱም በዚህ ገንዘብ የከተማው አስተዳደር ሊሠራ የሚችላቸው የልማት ሥራዎች የከተማው ነዋሪዎች (ወንድሜንም ጨምሮ) ተጠቃሚ መሆናቸው ይገባዋል፡፡ ስለዚህ የከተማው አስተዳደር የቦታ ግብርና ኪራይ ለመክፈል የሚመጡትን ሰዎች በትንሹም በትልቁም ከማጎሳቆል ይልቅ የታክሱን መጠን አሻሽለውና አስተካክለው አገልግሎታቸውን በተቀላጠፈ መንገድ ቢያበረክቱ ግብርና ኪራይ ከፋዩም ነዋሪዎቹም ደስተኛ ይሆናሉ፡፡ የከተማ አስተዳደሩም ለልማት የሚሆን ገንዘብ ተጨማሪ ያገኝና ሥራውም ይሳካለታል፡፡ ሁሉም አሸናፊ ይሆናል፡፡

ይህንን ለማድረግ የአስተዳደር ኃላፊነት ላይ የሚቀመጡ ሰዎች ቅንነትና ራዕይ ያላቸው የሕዝብ አገልጋይ ግለሰቦች መሆን አለባቸው፡፡ አለበለዚያ ልክ ያለፈው ታሪካችን እንደሚያሳየው የአገራችንን ዕጣ ፈንታ ቅንነትም ሆነ ራዕይ ለሌላቸው ፖለቲከኞችና ካድሬዎች ትተንላቸው ከክፋትና ከድንቁርና ቀንበር ሳንወጣ እየማቀቅን መኖር እንቀጥላለን፡፡ ትልቁ የአገር በደል ያለው እዚህ ላይ ነው፡፡

(አክሊሉ ኪዳኑ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ከአዲስ አበባ)

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የ ሳ ም ን ቱ ገ ጠ መ ኝ

ባለፈው ሰሞን ከቅርብ ጓደኛዬ ጋር ድሮ የምናውቃቸው ሰው ከዚህ ዓለም በሞት በመለየታቸው ለቅሶ ለመድረስ ኮልፌ እንሄዳለን፡፡ የሟች ቤተሰቦችን ለማስተዛዘን ከቅርብና ከሩቅ የመጡ ሰዎች ድንኳኑን...

የ ሳ ም ን ቱ ገ ጠ መ ኝ

ብዙዎቻችን የምናውቃቸው መጋቢ ሀዲስ እሸቱ በአንድ ስብከታቸው በምሳሌ ሲያስረዱ፣ ‹‹የደረቀ ጭንቅላት የለመለመ አገር ያደርቃል›› የሚለው አባባላቸው ቀልቤን ገዝቶታል፡፡ እሳቸው በአንድ ወቅት ወደ ዱባይ ሲሄዱ...

የ ሳ ም ን ቱ ገ ጠ መ ኝ

ለእኔ የሕይወት ፍልስፍና ከሚባለው ይልቅ የሕይወት መርህ ትክክለኛው ይመስለኛል፡፡ በዚህም ምክንያት ‹‹ነፃነቱን በእጅጉ የሚፈልግ ግዴታውንም ጠንቅቆ መረዳት አለበት›› የሚለው አባባል የሕይወቴ መርህ ነው፡፡ እኔ...

የ ሳ ም ን ቱ ገ ጠ መ ኝ

ገጠመኜን የምጀምረው ከበርካታ ዓመታት በፊት በሰማሁት ቀልድ መሳይ ምሬት ነው፡፡ ሰውዬው በአንድ ጉልበተኛ በደል ተፈጽሞበት አቤቱታ ለማቅረብ ፍርድ ቤት ይሄዳል፡፡ ፍርድ ቤት ክስ ማቅረብ...

የ ሳ ም ን ቱ ገ ጠ መ ኝ

ብዙ ጊዜ ትኩረት የማንሰጠው ችግር በቤተሰብ ውስጥም ሆነ በሥራ አካባቢ እየገጠመን ነው፡፡ እኔም ከመኖሪያ ሠፈሬ ጀምሮ እስከ መሥሪያ ቤቴ ድረስ ግራ የሚያጋቡ ሰዎች ያጋጥሙኛል፡፡...

የ ሳ ም ን ቱ ገ ጠ መ ኝ

ባለፈው ሳምንት እሑድ አንድ የማውቃቸው ትልቅ ሰው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተው ቀጨኔ መድኃኔዓለም የቀብራቸው ሥነ ሥርዓት ታዳሚ ነበርኩ፡፡ ከቀብሩ በኋላ ቤታቸው ሄጄ ቤተሰብ አስተዛዝኜ...

አዳዲስ ጽሁፎች

መንግሥት ገቢ ከመሰብሰብ ባሻገር ለሕዝብ ኑሮ ትኩረት ይስጥ!

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ ያለበት በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ከሚሰበሰብ ታክስ ብቻ ሳይሆን ከግብርና፣ ከኢንዱስትሪ፣ ከማዕድን፣ ከአገልግሎትና ከሌሎች ሀብት አመንጪ ዘርፎች ጭምር ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቁጥራቸው...

የኢትዮጵያን ትንሳዔ ለማብሰርና ለመከወን ምን እናድርግ?

በጌታነህ አማረ ኢትዮጵያ ማለት ታላቅ አገር ቀደምት የሰው ዘር መገኛና የሥልጣኔ ባለቤት የሆነች አገር እንደነበረች ታሪክ ሲያወሳን ይኖራል። በዚያውም ልክ ይህች ታላቅ ነበረች የምትባል አገር...

የምድራችን (የሰው ልጆች) ተማፅኖ — አረንጓዴ ፖለቲካ!

(ወጥመዶችና ማምለጫችን) በታደሰ ሻንቆ የወጥመዶች ዓለም በአፍሪካ ቀንድ አገሮች ዘንድ ያሉ ውዝግቦችና ግጭቶች ምንም ተቀባቡ ምን፣ መሬትን ውኃን አፈርን ማዕድናትን ንግድንና መሰል ጥቅሞችን የተመለከቱ ናቸው፡፡ በእነዚህ...

‹‹መንግሥት ከሁሉም ነገር በላይ ቅድሚያ ሰጥቶ የኢኮኖሚ ጫናውን ለመቀነስ የነዳጅ ድጎማውን መቀጠል ይኖርበታል›› ሰርካለም ገብረ ክርስቶስ (ዶ/ር)፣  የነዳጅ ዘርፍ ከፍተኛ ባለሙያ

የነዳጅ ግብይት ሥርዓትን ለመዘርጋትና ለመቆጣጠር ያስችላል የተባለ አዲስ አዋጅ ባለፈው ሳምንት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቋል፡፡ በኢትዮጵያ በነዳጅ ሥርጭት ግብይትና በአጠቃላይ በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች...

ስለካፒታል ገበያ ምንነትና ፋይዳ ያልተቋረጠና የተብራራ መረጃ ማድረስ ያሻል!

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ ሥራ ጀምሯል፡፡ አገራዊ ኢኮኖሚውን ከመደገፍና ለተለያዩ ኢንቨስትመንቶች የሚውል ካፒታል ለማሰባሰብ እንደ አንድ አማራጭ የሚወሰድና ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ ምዕራፍ የሚታይ ዕርምጃ...

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተያዘለት የሥነ ተዋልዶ ጤና ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተከሰቱ ጦርነቶችና ግጭቶች ምክንያት እየተስተጓጎለ የመጣውን የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት መልሶ ለማጠናከር ያስችላል የተባለ የ1.28 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን