Tuesday, December 5, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -

[ክቡር ሚኒስትሩ በስንዴ ምርት የተገኘው ውጤት የሕዝባችንን የምግብ ፍላጎት የሚመልስ ብቻ ሳይሆን ለአገር ክብርና ኩራት የፈጠረ መሆኑን ሲገልጹ አማካሪያቸው ደግሞ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚሰማውን ትችት እያካፈላቸው ነው] 

ቀን:

  • የስንዴ ምርት ልማቱ ጥሩ ቢሆንም አንዳንዶች ትችት እያቀረቡበት ነው።
  • ምን ብለው ተቹ
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ጤፍ እንጂ ስንዴ አዘውትሮ አይመገብም እያሉ ነው።
  • ድርቅና ረሃብ ሲገጥመን ግን የሚያቀርቡልን ዕርዳታ ስንዴ ነው። አይደለም እንዴ?
  • ልክ ነው። ግን እነሱ ምክንያታዊነት አያስጨንቃቸውም።
  • እንዴት?
  • በቃ መቃወም ከፈለጉ መቃወም ነው። ለዚያውም እስከ ጥግ ድረስ ሔደው የማይገናኝ አገናኝተው ነው የሚቃወሙት።
  • ለምሳሌ?
  • ሌላ ምሳሌ አያስፈልገንም። በዚሁ የሰንዴ ልማት ላይ ምን እያሉ መሰለዎት?
  • እ …
  • ለኢትዮጵያ ሕዝብ አስበው አይደለም።
  • እና ለማን ነው?
  • ለራሳቸው ነው።
  • ለእኛ ምን ያደርግልናል?
  • ሥልላጣናቸውን ለማራዘም።
  • ኦ..ኦ.. እዚህ ድረስ ዝቅ ብለዋል?
  • ለእኔም ግራ ገብቶኛል።
  • ምኑ ነው ግራ ያጋባህ?
  • ለምን በዚህ ደረጃ ለመቃወም እንደፈለጉ ለመረዳት ተቸግሬያለሁ። አንዳንዶቹ እኮ የሚናገሩት ግራ ያጋባል ክቡር ሚኒስትር?
  • ምን ይላሉ?
  • በዚህ መጠን የሰንዴ ልማት ውስጥ መግባት ተፅዕኖ እንደሚያመጣ ሳይረዱ ቀርተው አይደለም። አውቀው ነው እያሉ ነው።
  • ምን ተፅዕኖ ያመጣል ነው የሚሉት?
  • ሌሎች አዝዕርቶች በኢትዮጵያ እንዳይመረቱ ያደርጋል እያሉ ነው።
  • ምን?
  • አዎ። ሌሎች አዝዕርቶችን ለማጥፋት ነው እስከማለት ደርሰዋል።
  • ይደንቃል። ስንዴ ላይ ይህን ያክል ተቃውሞ?
  • በዚህ ጭፍን ተቃውሞ ከቀጠሉ በቅርቡ አንድ ነገር ማለታቸው አይቀርም፡፡
  • ምን ሊሉ ይችላሉ?
  • ጄኖሳይዳል ነው።
  • ምኑ?
  • የሰንዴ ልማቱ!

[ክቡር ሚኒስትሩ የሰሜኑን ግጭት ለመፍታት የተጀመረውን ድርድር በተመለከተ ከአማካሪያቸው ጋር ሐሳብ እየተለዋወጡ ነው]

  • የአንድ ድርድር ውጤታማነት በመጀመሪያዎቹ ቀናት ሁኔታ ወይም ውጤት ይለካል ብሎ ማሰብ ትክክል ይመስልሃል?
  • እሱን እረዳለሁ ክቡር ሚንስትር። በእኛ ሁኔታ ግን ከሁለት አንዱ መስመር መያዝ ነበረበት።
  • ከሁለት አንዱ ማለት?
  • ወይ ድርድሩ ወይም ደግሞ በግንባር ያለው ሁኔታ መስመር መያዝ ነበረበት ማለቴ ነው።
  • ስንዴ እየዘራን መሰለህ እንዴ?
  • ኧረ ስለ ስንዴ አላወራሁም?
  • ታዲያ ምንድን ነው መስመር መስመር …መስመር መያዝ አለበት የምትለው?
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ ብቻ ሳልሆን ማኅበረሰቡ ጭምር ቅር ብሎታል።
  • ለምን?
  • አለቃ ሰሞኑን ለውጭ ሚዲያ ስለድርድሩ በሰጡት ቃለ ምልልስ ነው።
  • አላየሁትም። ምን አሉ?
  • አንደኛው ነጥብ የውጭ ጣልቃ ገብነት በዝቷል የሚል ነው።
  • እሺ …
  • የውጭ ጫና ከበዛ ሰላም ሩቅ ይሆናል በማለት ጫና መኖሩን ጠቁመዋል።
  • እውነት ነው። የውጭ ጣልቃ ገብነትና ጫናው ከፍተኛ ነው።
  • ክቡር ሚኒስትር ይህንንማ ራሳችን የፈቀድነው በመሆኑ ጫና እንደሚመጣ ወይም ጫናውን እንደምናመክነው መጀመሪያውኑ ማወቅ ነበረብን።
  • እንዴት?
  • የአፍሪካ ኅብረትም ይሁን ሌላ እንዲያደራድሩን የተስማማነው በፈቃዳችን አይደለም እንዴ?
  • እሱማ ነው!
  • ታዲያ አሁን ላይ የውጭ ጣልቃ ገብነትና ጫና ብለን መቃወም ተገቢ ነው?
  • ነገሩ አልገባህም። ምን መሰለህ?
  • እ …
  • አደራዳሪዎቹ አይደለም ጣልቃ እየገቡ ያሉት።
  • ማነው?
  • ታዛቢዎቹ ናቸው። ድርድሩም የተራዘመው በእነሱ ሴራ ነው፡፡
  • እንዴት?
  • መንግሥት ቡድኑ ትጥቅ መፍታት አለበት በሚለው አቋሙ ፅኑ ነበር።
  • እሺ …?
  • ቡድኑ ደግሞ በተቃራኒው ትጥቅ እንደማይፈታ ሽንጡን ገትሮ ሲሟገት የድርድሩ ማብቂያ ደረሰ።
  • እሺ …?
  • በኋላ ከታዛቢዎቹ ጋር ተመካክሮና ማስተማመኛ አግኝቶ አንድ ጉዳይ ይዞ መጣ።
  • ምን ይዞ መጣ?
  • ትጥቅ ለመፍታት እስማማለሁ አለ።
  • መጨረሻ ላይ?
  • አዎ።
  • እሺ የእኛ ተደራዳሪዎች ምን አሉ?
  • የእኛ ተደራዳሪዎች ምላሽ ከመስጠታቸው በፊት ታዛቢዎቹ በጉዳዩ በጥልቀት ለመነጋገር የድርድሩ ጊዜ መራዘም አለበት አሉ።
  • እሺ ከዚያስ?
  • ነገሩ የአቋም ለውጥ በመሆኑ የድርድር ጊዜው ተራዝሞ ውይይት ይደረግ ተባለ።
  • እሺ?
  • ወደ ዝርዝሩ ሲገባ ግን አዲስ ነገር የለም።
  • እንዴት?
  • ቡድኑ ትጥቅ ለመፍታት እስማማለሁ ነገር ግን ይህንን ተግባር የምፈጽመው በድርድሩ መጨረሻ ላይ ነው አለ።
  • ምን …?
  • አዎ። ትጥቅ ለመፍታት ዝግጁ ነኝ ግን ትጥቅ መፍታት አንዴ የሚተገበር ነገር አይደለም ስለዚህ ጊዜ ተወስዶ መፈጸም አለበት። እስከዛ ግን በሌሎች ጉዳዮች ድርድሩ ይቀጥል አለ።

ጊዜ መግዣ መሆኑ ነው?

  • እንደዚያ ነው። ግን የቡድኑ አይደለም የሚገርመው።
  • እ …?
  • የታዛቢዎቹ ነው።
  • ለምን?
  • ቡድኑ ትጥቅ ለመፈታት መስማማቱ አንድ ትልቅ ዕርምጃ በመሆኑ በእናንተ በኩልም አንድ ዕርምጃ መምጣት አለባችሁ አሉ።
  • ምን ጠየቁ?
  • ተኩስ ማቆም አለባችሁ!
  • ወደፊት ትጥቅ እፈታለሁ ስላለ?
  • አዎ። ለዚያ ነው አለቃ የውጭ ጣልቃ ገብነትና ጫና በዝቷል ያሉት፡፡
  • አሁን ግልጽ ሆኖልኛል ቢሆንም ግን …
  • ግን ምን?
  • አለቃ የተናገሩት ጫና ስለመብዛቱ ብቻ አይደለም።
  • ሌላ ምን ብለዋል?
  • ችግራችንን እኛው መፍታት እንችላለን ብለዋል።
  • እንደዚያ ያሉት ጣልቃ ለሚገቡት የውጭ ኃይሎች ነው።
  • እኔ ግን እንደዚያ ለማለት የፈለጉ አልመሰለኝም።
  • ምን ለማለት የፈለጉ ነው የመሰለህ?
  • እኛው እንታረቅ ያሉ አስመስለው ሌላ ነገር ለማለት የፈለጉ ነው የመሰለኝ።
  • ምን?
  • ገላጋይ አይግባ!

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...