Wednesday, March 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናቅዱስ ሲኖዶስ ሦስቱን ጳጳሳት ስልጣነ ክህነታቸውን አንስቶ አወገዘ

ቅዱስ ሲኖዶስ ሦስቱን ጳጳሳት ስልጣነ ክህነታቸውን አንስቶ አወገዘ

ቀን:

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ሰሞኑን ጥር 14 ቀን 2015 ዓም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሃገረ ስብከት በሶዶ ዳጬ ወረዳ ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ፣ የቤተክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 26 ኤጲስቆጶሳትን በመሾማቸውና ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በመገናኛ ዘዴዎች በማስነገራቸውና ክህደት በመፈጸማቸው፣ አባ ሳዊሮስ፣ አባ አዎስጣጤዎስና አባ ዜናማርቆስ ከድቁና ጀምሮ ያለው ክህነተ ስልጣናቸውን አንስቶ አወገዘ።

ቅዱስ ሲኖዶስ እንዳስታወቀው፣ የወሊሶውን ሕገ ወጥ የኤጴስ ቆጶሳት ሹመት ያስፈጸሙት ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ግለሰቦችና ሕገ ወጥ ሹመቱን ለመቀበል ወሊሶ የሄዱ 26 መነኮሳት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአንድነት ጉባኤ ተለይተው እንዲወገዙ ወስኗል።

 ፓትርያርክ ባለበት ሉዋላዊ ስልጣንን በመግፋትና መፈንቅለ ሲኖዶስ በማድረጋቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል። ቅዱስ ፓትርያርክ በሌለበት የሚሰጥን ሹመትን ሲኖዶስ እንደሚያወግዝና ሲመቱም ሕገ ቤተ ክርስቲያን “የተወገዘ ይሁን” ስለሚል አውግዟል:: መጠርያቸውም ሊቀ ጳጳስና ቆሞስ ተብሎ ይጠራ የነበረው አቶ ተብሎ እንዲተካ በሙሉ ድምጽ ተወስኗል። ሕገ ወጥነት ሲመቱ እንዲፈጸም ያስተባበሩና ሥልጣነ ክህነት ያላቸው አካላት በሙሉ ተወግዘው ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነት እንዲለዩ በተጨማሪ ወስኗል።

በጸጸት የተመለሱት አባ ጸጋ ዘአብ ብቻ በውግዘት ሳይለዩ በልዩነት ተይዘው በቅኖና ቤተ ክርስቲያን ጉዳያቸው እንዲታይና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በጠበቀ መንገድ በይቅርታ ከተመለሱ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምትቀበላቸው መሆኑን አስታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...

አይ የእኛ ነገር!

የዛሬው ጉዞ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ነው፡፡ መንገዱ ለሥራ በሚጣደፉ፣...

የዓለም ኢኮኖሚ መናጋት ለወቅታዊው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ነው?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 16...