- Advertisement -

[ክቡር ሚኒስትሩ በወቅታዊ ፀጥታና ደህንነት ጉዳዮች ላይ የቀረበላቸውን ምክረ ሐሳብ እያደመጡ ነው]

  • ችግሩ ምን እንደሆነ በትክልል ለይተነዋል ግን
  • ግን ምን?
  • በይፋ መናገር አልነበረብንም።
  • ለምን?
  • ችግሩን ምን እንደሆነ በይፋ በመናገራችን ተዋናዮቹ ራሳቸውን ለመከላከል በየቦታው ግጭት እየቀሰቀሱብን ነው።
  • ታዲያ ምንድነው ማድረግ የሚሻለን ትላለህ?
  • ከእርሶ ባለውቅም አንድ ሐሳብ አለኝ።
  • ምንድነው ሐሳብህ?
  • የማይደፈር የሚባል አንድ ዓሳ ነባሪ ብንይዝ ሌላውን ማስደንገጥ ይቻላል
  • ጥሩ ሐሳብ ነው ግን …
  • ግን ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ዓሳ ነባሪው ማነው?
  • እሱ ላይ መነጋገር ይኖርብናል።
  • ምንድነው የምንነጋገረው?
  • ዓሳ ነባሪው ማን እንደሆነ ወይም …
  • ወይም ምን?

 

  • ማን እንደሚሆን!
  • ግን ደግሞ ለሕዝቡ ቃል የገባነው ነገር አለ?
  • ቃል የገባነው ምን አለ?
  • የመንግሥት ሌቦችን ለመመንጠር ብሔራዊ ኮሚቴ አቋቁመን ጥቆማ እንዲሰጠን ጠይቀንዋል።
  • ታዲያ ምን ችግር አለው … ይጠቁም!
  • ቶሎ ዕርምጃ መውሰድ ካልጀመርን ሕዝቡ ተስፋ ይቅርጥብናል ብዬ ሰግቼ ነው።
  • ሌሎች የሕግ ማስከበር ዕርምጃዎችን በመውሰድ ተስፋ እንሰጠዋለና ምን ችግር አለው።
  • ምን ዓይነት ‹‹ዕርምጃ ልንወስድ እንችላለን?
  • አንዳንድ ቤቶችን እናሽጋለን!
  • የምን ቤቶችን?
  • ሺሻ ቤቶችን!

[ክቡር ሚኒስትሩ ሰሞኑን ከምሑራን ጋር በተደረገው ውይይት ዙሪያ ከፖለቲካ ዘርፍ አማካሪያቸው ጋር ሐሳብ እየተለዋወጡ ነው]

  • ሰሞኑን ከዩኒቨርስቲ መምህራን ጋር የተደረገውን ውይይት ተከታተልክ?
  • አዎ፣ ተከታትያለሁ።
  • ምን ተሰማህ?
  • ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የተሰማኝ።
  • ድብልቅልቅ ስሜት ስትል ምን ማለትህ ነው?

 

  • በውይይቱ ወቅት የተገለጹት አንዳንድ ሐሳቦች ኃላፊነት የተሞላባቸውና ሕግን መሠረት ያደረጉ ናቸው።
  • እሺ፡፡
  • እንዳዶቹ ግን ሕጋዊነት የጎደላቸው እንዲሁም ግለኝነት የተጫናቸው ስለሆኑ ባይነገሩ እመርጥ ነበር።
  • ቆይ የትኞቹ ንግግሮች ናቸው እንዲህ ያስባሉህ?
  • በምሳሌ ልጥቀስልዎት?
  • ይሻላል …
  • ለምሳሌ ፓርቲያችን በሚቀጥለው ምርጫ ቢሸነፍና የፓርቲያችን ሰዎች ተሰብስበው እንዴት እንለቃለን ቢሉ በግሌ ወጥቼ ተሸንፌያለሁና ኑ ሥልጣን ተረከቡ ብዬ በይፋ እናገራለሁ ያሉት ተገቢና ኃላፊነት የተሞላበት እንዲሁም ሕጋዊነትን የተላበሰ ነው።
  • እሺ ሌላውስ?
  • ሌላው ሲሉ?
  • ባይነገር እመርጣለሁ ያስባለህን ማለቴ ነው።
  • አዎ። ይኼኛውም በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ የተሰጠ አስተያየት ነው።
  • በተመሳሳይ ስትል?
  • የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነትን የተመለከተ ነው ማለቴ ነው።
  • ምንድነው ያሉት?
  • ሕዝብ በድምፁ ከሰጠኝ የአምስት ዓመታት ኮንትራት ውስጥ ሦስት ዓመት ገደማ አለኝ። ከዚህ ውጪ የሚሆን ነገር የለም። በእነዚህ ሦስት ዓመታት ውስጥ ላሳካቸው የምፈልጋቸው ህልሞች አሉ የሚል ንግግር ተናግረዋል።
  • ታዲያ ይህን ማለታቸው ምን ችግር አለው? እውነት አይደለም እንዴ?
  • ሕዝብ በድምፁ ለአምስት ዓመት እንድንመራው መምረጡ እውነት ነው።
  • ታዲያ ችግር ያልከው ምንድነው?
  • አንደኛ ግለኝነት የተጫነው ንግግር ነው።
  • ምን ማለት ነው?
  • አንደኛ ሕዝብ ድምፁን የሰጠው ለፓርቲው እንጂ በግል ለእሳቸው አይደለም። ስለዚህ ፓርቲው እንጂ ሦስት ዓመት ያለው እሳቸው አይደሉም።
  • እሺ ሁለተኛውስ?
  • ሁለተኛ የምንከተለው ሥርዓት ፓርላሜንታራዊ ሥርዓት ነው።
  • ቢሆንስ?
  • ጥሩ። አንደኛ የመረጣቸው ሕዝብ ካመነበት ዛሬውኑ ውክልናውን በማንሳት ከፓርላማ ወንበራቸው እንዲነሱ ማድረግ ይችላል። ይህንን ሕጋዊ መብት በመጠቀም ውክልናውን ካነሳ ደግሞ ከፓርላማ ብቻ ሳይሆን የያዙትም ሥልጣን ያሳጣቸዋል።
  • ለምን?
  • ምክንያቱም የፓርላማ አባል ያልሆነ ሰው ሥልጣን መያዝ አይችልም። በሌላ በኩል ደግሞ …
  • እሺ በሌላ በኩል … ቀጥል …
  • ለዚህ ሥልጣን የመረጣቸው ፓርቲም በተመሳሳይ አስፈላጊ ነው ብሎ ካመነ ሌላ አባል መርጦ እሳቸውን መተካት ይችላል። በእርግጥ …
  • እህ … ቀጥል
  • ፓርቲው ይህንን ያደርጋል ማለት አይደለም ቢያስብም በቀላሉ የሚፈጸም አይደለም። ነገር ግን
  • ነገር ግን ምን?
  • ግላዊነትን የሚያጎላ ነገር ባይነገር ይሻላል።
  • ግላዊነት ስትል?
  • ሦስት ዓመት ይቀረኛል … ከዚያ በፊት ማንም ከሥልጣኔ ሊያነሳኝ አይችልም … ላሳካቸው የምፈልጋቸው ሕልሞች አሉኝ የሚሉ ነገሮችን ባይናገሩ ማለቴ ነው።
  • ምን ቢሉ ይሻል ነበር?
  • ገዢው ፓርቲ ሦስት ዓመታት ይቀሩታል … ሊያሳካቸው የሚፈልጋቸው ሕልሞች አሉት … ገዢው ፓርቲ በመጪው ምርጫ ከተሸነፈ ሳያቅማማ ሥ
  • ልጣን ይለቃል ቢባል የተሻለ ነው።
   

 

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ አባላቱ የተከበሩ ተብለው የሚጠሩት በምክንያት አይደለም እንዴ? ትክክል ነው። ምክንያቱም፣ ምክር ቤቱ ትልቁ የሥልጣን አካል ነው፣...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...

[የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣን በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመመካከር በሚኒስትሩ ቢሮ ተገኝተው ውይይታቸውን ጀምረዋል]

ክቡር ሚኒስትር ባላንጣዎቻችን የእኛኑ ስልት መጠቀም የጀመሩ ይመስላል። እንዴት? ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ? እስከዛሬ እኛ የምንሰጣቸውን አጀንዳ ተቀባይ ነበሩ። በዚህም በውስጣቸው ልዩነትንና አለመግባባትን መትከል ችለን ነበር። አሁን...

[ክቡር ሚኒስትሩ ጠዋት ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ጸሐፊያቸው ሰሞኑን በአባቶች መካከል ስለተደረገው ስምምነት ጠየቀቻቸው።]

ደህና አደሩ ክቡር ሚኒስትር? ሰላም። ልታወሪኝ የፈለግሽው ነገር ያለ ይመስላል? አዎ። እንዲያው ነገሩ ግርም ቢለኝ ልጠይቅዎ አስቤ ነው ክቡር ሚኒስትር። ምንድነው? ሰሞኑን አባቶችን አስማምታችሁ አልነበርም እንዴ? ልክ ነው። ቤተ...

አዳዲስ ጽሁፎች

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ አባላቱ የተከበሩ ተብለው የሚጠሩት በምክንያት አይደለም እንዴ? ትክክል ነው። ምክንያቱም፣ ምክር ቤቱ ትልቁ የሥልጣን አካል ነው፣...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል መንግሥታት አመራሮችን ይዘው የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር)፣ ግፊቱ እየጨመረ...

አይ የእኛ ነገር!

የዛሬው ጉዞ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ነው፡፡ መንገዱ ለሥራ በሚጣደፉ፣ የእለት ጉርሳቸውን ምፅዋት ለማግኘት ለወጪ ወራጁ እጃቸውን በሚዘረጉ፣ ኑሮ ይሁን ወይም የዘመኑ ሁኔታ አቅላቸውን አሳጥቷቸው...

የዓለም ኢኮኖሚ መናጋት ለወቅታዊው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ነው?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ያለፉትን ስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም የተመለከተ ማብራሪያ...

የተዘነጋው የከተሞች ሥራ የመፍጠር ተልዕኮ

በንጉሥ ወዳጅነው አሁን አሁን የአገራችን የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ አንገብጋቢና ሊታሰብበት የሚገባ አጀንዳ እየሆነ ነው፡፡ ከዓመት ዓመት እየተጠራቀመ ከመጣው ተምሮ ቁጭ ካለ ኃይል አንፃር ብቻ...

ሆድና የሆድ ነገር

(ክፍል ስድስት) በጀማል ሙሐመድ ኃይሌ (ዶ/ር) አቶ ባል - "ለዛሬ ገንፎ"    ወ/ሮ ሚስት - "ለልክህ ድፎ" ዜናዎች ወይም በአጠቃላይ መረጃዎች በጋዜጣ ላይ ከመታተማቸው፣ በሬዲዮና በቴሌቪዥን ከመሠራጨታቸው በፊት...

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን