Sunday, March 26, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ስለፖለቲካ ማርኬት ፕሌስ ጽንሰ ሐሳብ አጥንተው ከፍተኛ አመራሮችን ሲያሠለጥኑ ቢሰነብቱም ዛሬ ከባለቤታቸው የተነሳውን ጥያቄ ለመመለስ ተቸግረዋል]

  • እኔ ምልህ ክቡር ሚኒስትር?
  • ክቡር ሚኒስትር ካልሽኝ ችግር አለ ማለት ነው።
  • ችግርማ አለ።
  • እሺ … እኔ ምልህ ያልሽው ለምን ነበር?
  • ልጠይቅህ ነዋ።
  • ምን?
  • ከጥቂት ሳምንታት በፊት ስትሰብኩት የነበረው ነገር የውሸት ነው ማለት ነው?
  • ምን ሰበክን?
  • በመጀመሪያ የፓርቲ አባሎቻችሁን ቀጥሎ ማኅበረሰቡን ስለፖለቲካ ማርኬት ፕሌስ ወይም ስለፖለቲካ ገበያ ስትግቱ አልነበረም እንዴ?
  • አዎ፣ ስለአገሪቱ የፖለቲካ ገበያ መበላሸት ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ አሁንም እየሠራን ነው።
  • ግን እናንተ ራሳችሁ ስለጽንሰ ሐሳቡ ግንዛቤ አላችሁ?
  • እንዴት? ምን ዓይነት ጥያቄ ነው?
  • መንግሥት ራሱ የፖለቲካ ሸቀጥ ይዞ ገበያ መውጣቱን ስመለከት ጊዜ ግራ ገብቶኝ ነዋ፡፡
  • መንግሥት እንዴት እንደዚህ ያደርጋል? ጽንሰ ሐሳቡ አልገባሽም ማለት ነው?
  • የፖለቲካ ገበያ ማለት የፖለቲካ ሥልጣን ለመያዝ ወይም የመንግሥትን ሥልጣን ለማፅናት ለገበያ የሚያቀርብ ሸቀጥ አይደለም እንዴ?
  • ትክክል ነሽ፣ አንዱ መገለጫው እሱ ነው።
  • ሥልጣንን ለማፅናት የብሔር ወይም የሃይማኖት ድጋፍ ለማግኘት መትጋት የፖለቲካ ሸቀጥ አይደለም?
  • ነው እንጂ፣ እንዲያውም አደገኛው እሱ ነው።
  • የፖለቲካ ገበያው መበላሸት የሚያስከትለው ውጤት ተቋምን፣ ቀጥሎም አገርን የማፍረስ አደጋ ያስከትላል ስትሉም ሰምቻለሁ አይደል?
  • ትክልል ነሽ? ይህ አዝማሚያ አደገኛ ነው ያልንበት ምክንያት አገር ስለሚያፈርስ ነው።
  • ታዲያ አገር በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ላይ ለምን መዝመት ፈለጋችሁ?
  • እሱ እንኳን ከዚህ ጋር አይገናኝም።
  • እንዴት አይገናኝም?
  • የሃይማኖት ጉዳይ ስለሆነ።
  • የሃይማኖት ጉዳይ ብቻ እንዳልሆነማ ግልጽ ነው።
  • እንዴት?
  • ነገሩ የሲኖዶሱን አብላጫ ለመቆጣጠር ወይም አገር ናት ያላችኋትን ተቋም ለመከፋፈል የሚደረግ ጥረት ነው።
  • ለምን ብለን እንደዚያ እናደርጋለን?
  • ለማፅናት ፈልጋችሁ ይመስለኛል።
  • ምን ለማፅናት?
  • ሥልጣናችሁን፡፡
  • በፍፁም፣ ተሳስተሻል፡፡
  • ታዲያ ለምን ችግሩን ለመፍታት ሰነፋችሁ?
  • ሰንፈን አይደለም።
  • እና ምን ሆናችሁ ነው?
  • መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባት ስለማይችል ነው።
  • ታዲያ ለምን እናንተ ገባችሁ?
  • አልገባንም?
  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማትን እየሰበሩ መቆጣጠር የጀመሩትን እያያችሁ ዝም ማለታችሁ እኮ ያው ነው።
  • ያው ነው ማለት?
  • ጣልቃ መግባት ነው፡፡
  • በፍፁም! የመንግሥት ፍላጎት ራሳቸው ተነጋግረው ልዩነታቸውን እንዲፈቱት ብቻ ነው።
  • የአዲስ አበባ ባለአደራ አስተዳደር በሚል ተጀምሮ የነበረውን እንቅስቃሴ ታስታውሳለህ?
  • አዎ፣ እሱን በምን አስታወሽው?
  • በወቅቱ የነበረው ጭንቀታችሁ ትዝ ብሎኝ ነው።
  • በአንድ ከተማ ላይ ሁለት አስዳደር ለመፍጠር መሞከር ትክልል አይደለም፣ በዚያ ላይ አካሄዱ አስፈሪ ነበር።
  • ቢሆንም ከማሰር ይልቅ በውይይት ብትፈቱት ይሻል ነበር።
  • እንዴት አድርገን ነው ከእነሱ ጋር የምንወያየው?
  • አሁን የቤተ ክርስቲያን ችግር በውይይት ይፈታል እንዳልከው።
  • እሱ ሌላ! ያ ሌላ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ከውጭ ይገቡ የነበሩ 38 ዓይነት ምርቶች እንዳይገቡ ዕግድ ተጣለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 38 ከውጪ የሚገቡ ምርቶች ላይ ዕገዳ...

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ18 ቀናት ግዢ መፈጸሚያ ብቻ እንደሚሆን አይኤምኤፍ ተነበየ

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ0.6 ወር ወይም...

ጉራጌን በክላስተር ለመጨፍለቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚቃወም ጎጎት ፓርቲ አስታወቀ

ለጉራጌ ሕዝብ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር እንደሚታገል የሚናገረው አዲሱ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...