Saturday, September 23, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅ‹‹ሳል ይዞ ስርቆት ቂም ይዞ ጸሎት በሚለው ላይ ስንፍ ይዞ ድርሰት የለም››

‹‹ሳል ይዞ ስርቆት ቂም ይዞ ጸሎት በሚለው ላይ ስንፍ ይዞ ድርሰት የለም››

ቀን:

ለደራስያን በሙሉ የምመክረው አንድ ነገር አለ፡፡ ንቃትም፣ ትጋትም ያጠጠበት ዘርፍ መስሎ የታየኝ ነገር ስላለ፡፡ ድርሰት ትልቅ ዝግጅትን ይጠይቃል፡፡ ከዝግጅቶቹ አንዱና መሠረታዊው ዕውቀትን በመመልከት፣ ዙሪያን በመቃኘት፣ በተለይ ደግሞ በማንበብና ያነበቡትን አጣጥሞ ራስን በመመርመር አዕምሮን ከልቡና ጋር ማዳበር ነው፡፡ ዝም ብለን፣ አንድ ቀን ወፈፍ ጨምደድ ያደረገን ዕለት ተነሥተን እስቲ ወደ ገበያ ልውጣ እንደሚባለው፣ እስቲ ድርሰት ልጻፍ አይባልም፡፡

ድርሰት ከባዶ ስለማይፈልቅ፣ ያለፉትን፣ የቀደሙትን ዘመናትና ደራስያን ድርሰቶችን ማንበብ ያስፈልጋል፡፡ ሳል ይዞ ስርቆት ቂም ይዞ ጸሎት በሚለው ላይ ስንፍ ይዞ ድርሰት የለም የሚለውን እጨምራለሁ፡፡ አፈ ታሪኩን፣ ተረታ ተረቱን፣ ሚቶሎጂውን፣ ሃይማኖታዊ መጻሕፍቱን፣ ታሪክን፣ ፍልስፍናን ማንበብ ለደራሲ የምርጫ ጥያቄ መሆን ያለበት አይመስለኝም፣ ሙያዊ ግዴታም፣ የሰብዓዊነት መርህም እንጂ፡፡ ዕውቀታችን ግልብ ከሆነ፣ ድርሰታችን እንደዚያው ቀላል ይሆናል፡፡ ስለዚህ የንባብ ዋጋ ከመድረስ ዋጋ ቢበልጥ እንጂ አያንስምና ቀደምት ድርሰቶች ዘርታችሁ ልታፈሩ ላሰባችኋቸው ድርሰቶች ግብዓት ይሁኗችሁ፡፡

– ዮናስ አድማሱ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ‹‹መድበለ ጉባኤ›› (2001)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...