ከሰማንያ ስድስት ዓመታት በፊት፣ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. በፋሺስት ጣሊያን የተጨፈጨፉ ኢትዮጵያውያን ሰማዕታት መታሰቢያ የካቲት 12 ቀን 2015 ዓ.ም. ታስቧል፡፡ በተለይ ለሰማዕታቱ መታሰቢያ በስድስት ኪሎ በቆመው ሐውልት ሥር፣ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፡፡ የጥንት አርበኞች፣ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ተማሪዎች በተገኙበት መታሰቢያው ሲከናወን፣ ወታደራዊ ሠልፍ፣ የአርበኞችና የተማሪዎች ሠልፍና ትርዒት የቀረበ ሲሆን የመከላከያና የፌዴራል ፖሊስ ማርሽ ባንዶች ጣዕመ ዜማ አሰምተዋል፡፡ ፎቶዎቹ የአከባበሩን ገጽታ ያሳያሉ፡፡
- ፎቶ የከንቲባ ጸሕፈት ቤት