Sunday, March 26, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ጠዋት ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ጸሐፊያቸው ሰሞኑን በአባቶች መካከል ስለተደረገው ስምምነት ጠየቀቻቸው።]

  • ደህና አደሩ ክቡር ሚኒስትር?
  • ሰላም። ልታወሪኝ የፈለግሽው ነገር ያለ ይመስላል?
  • አዎ። እንዲያው ነገሩ ግርም ቢለኝ ልጠይቅዎ አስቤ ነው ክቡር ሚኒስትር።
  • ምንድነው?
  • ሰሞኑን አባቶችን አስማምታችሁ አልነበርም እንዴ?
  • ልክ ነው። ቤተ መንግሥት ጠርተን እንዲወያዩ አድርገን አስማምተናቸዋል።
  • እንዲያውም የጠፉትን በጎች ይዘን መጥተናል ብላችሁ ስትወስዷቸው በቴሌቪዥን ሁሉ ተላልፎ ነበር።
  • ልክ ነው።
  • ታዲያ ለምን ተመልሰው ወጡ።
  • ወጡ ማለት?
  • ስምምነቱን አፈረሱት።
  • አያደርጉትም?
  • አድርገውታል። እንዲያውም መግለጫ ሁሉ ሰጥተዋል።
  • ቤተ መንግሥት ድረስ ጠርተን አስማምተናቸው? አያደርጉትም!
  • የቤተ መንግሥቱ ካልሆነ ሌላ ቦታ ውሰዷቸው?
  • የት?
  • ፕሪቶሪያ!

[ፓርቲው ያፀደቃቸውን አገር አሻጋሪ መርሆች እንዲያሰርጹ ሁሉም የፓርቲው አባላት በታዘዙት መሠረት ክቡር ሚኒስትሩ ከቤታቸው ቢጀምሩም ባለቤታቸው የዋዛ ሆነው አልተገኙም]

  • የፓርቲያችን መርሆች እንደ አገር ለማሳካት ለምንፈልጋቸው ትልሞችና ለጀመርነው የለውጥ ሒደቶች ከፍተኛ አቅም እንደሚሆኑ ጥርጥር የለኝም።
  • ምኖች ነው ያልከው?
  • መርሆች።
  • ምንድናቸው?
  • አራት ናቸው።
  • ምን ምን?
  • አንደኛው መርህ፣ የዜጎች ክብር ነው!
  • ሁለተኛውስ?
  • ሁለንተናዊ ብልፅግና ለዜጎች!
  • እህ … ቀጣዩስ?
  • ነፃነትና እኩልነት!
  • እሺ … አራተኛውስ?
  • ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት
  • ምን እማማችነት?
  • ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት።
  • እሱ ብቻ ነው የሚቻለው?
  • የሚቻለው ማለት?
  • ማለቴ ከወንድማማችነትና እህትማማችነት ውጪ ሌላ ነገር አይኖርም።
  • ሌላ ነገር ማለት?
  • ኅብረ ብሔራዊ ጋብቻ?
  • ለምን ታፌዣለሽ?
  • እህ … እኔስ ከማን አንሳለሁ?
  • ከማን አንሳለሁ ማለት?
  • እናንተ ስታፌዙ ማለቴ ነው።
  • ወደ ብልፅግና የሚያስፈነጥሩን መርሆች ናቸው አልን እንጂ መቼ አፌዝን?
  • ተው … ተው …
  • ለምን?
  • የምትሉትና የምትተገብሩት ነገር አይገናኝማ? የተለያየ ነው።
  • የቱ ጋ ተለያየ?
  • ከምታደርጉት አንዱን ወስደህ ብትፈትሽ ታገኘዋለህ።
  • ምኑን ልፈትሽ?
  • ሰሞኑን በወልቂጤ ከተማ የተፈጸመውን ድርጊት ብትፈትሽ ልዩነቱን ታየዋለህ።
  • የምኑን ልዩነት?
  • ያስፈነጥሩናል በምትሏቸው መርሆችና በምትተገብሩት መካከል ያለውን ልዩነት።
  • ጥሩ፣ እንፈትሽ። ግን በወልቂጤ ምንድነው የተፈጠረው?
  • የገጠማቸው የመጠጥ ውኃ ችግር እንዲታወቅላቸው ሠልፍ በወጡ ነዋሪዎች ላይ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች ጥይት ተኩሰው ሦስቱን ገደሉ።
  • አልሰማሁም።
  • ሰላማዊ ሠልፍ የወጡት እንኳን እንዳንተ አልሸሹም።

 

  • እኔ እየሸሸሁ አይደለም። አልሰማሁም።
  • ባትሰማውም ይኸው አሁን ሰምተሃል።
  • እሺ … በወልቂጤ የተፈጸመውን በማነጻጸር መርሆቹን እንድፈትሽ ነው ያልሽው አይደል?
  • አዎ።
  • እሺ ቀጥይ … እንፈትሽ።
  • መርህ አንድ የዜጎች ክብር ነው አይደል?
  • አዎ።
  • ከዚህ መርህ አንፃር የመጠጥ ውኃ የጠየቁ ነዋሪዎች ላይ ጥይት ተኩሶ መግደል የዜጎች ክብር መገለጫ ነው? ተገቢ ነው?
  • አይደለም።
  • መርህ ሁለት ሁለንተናዊ ብልፅግና ነው አይደል?
  • አዎ።
  • የመጠጥ ውኃ ማግኘት መሠረታዊ የዜጎች መብት አንጂ የብልፅግና ጥያቄ አይደለም።
  • እውነት ነው።
  • ይህንን መሠረታዊ መብት ጥያቄ ሳይመልሱ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ማረጋገጥ ይቻላል?
  • አይቻልም።
  • መርህ ሦስት። ነፃነትና እኩልነት ነው። የወልቂጤ ነዋሪዎች ከሌሎች ከተሞች ነዋሪዎች ዕኩል የመጠጥ ውኃ ሊቀርብላቸው አይገባም?
  • ይገባል! ግን..
  • ቆይ ቆይ። የወልቂጤ ነዋሪ የገጠመውን ችግር የመግለጽና ተቃውሞ የማሰማት ነፃነት የለውም።
  • ነፃነትማ አለው፣ ነገር ግን …?
  • ግን ምን?
  • ሠልፉ የተፈቀደ መሆን አለበት?
  • መርህ አራት። ሕዝብን ቅራኔ ውስጥ እየከተትክ የሚፈጠር ወንድማማችነትም በለው እህትማማችነት አይኖርም። አራት ነጥብ።
  • በእርግጥ ስለ መርሆቹ አተገባበር ያነሳሽው በሙሉ ትክልል ነው። ጉድለት አለበት። ነገር ግን …
  • ‹‹ነገር ግን›› ካላችሁ ማምለጫ እየፈለጋችሁ እንደሆነ ይታወቃል።
  • በፍፁም አይደለም።
  • እሺ … ግን ምን?
  • የመርሆቹ አተገባበር ላይ ያነሳሽው ትክክል ነው። ግን መረዳት ያለብሽ እኛም አንቺ ያልሽውን ነው ያልነው።
  • እናንተ ምንድነው ያላችሁት?
  • ኢትዮጵያን ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና ማስፈንጠር የምንችለው በእነዚህ መርሆች ብቻ አይደለም ብለናል።
  • ታዲያ ሌላ በምንድነው?
  • መርሆቹን በአግባቡ መተግበር ስንችል ነው!
  • ለምን ትደረድራላችሁ ታዲያ?
  • ምን?
  • መርህ!

–         

–         

 
     

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ከውጭ ይገቡ የነበሩ 38 ዓይነት ምርቶች እንዳይገቡ ዕግድ ተጣለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 38 ከውጪ የሚገቡ ምርቶች ላይ ዕገዳ...

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ18 ቀናት ግዢ መፈጸሚያ ብቻ እንደሚሆን አይኤምኤፍ ተነበየ

ኢትዮጵያ በ2023 የሚኖራት የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለ0.6 ወር ወይም...

አስተዳደሩ ይዞታን ለማረጋገጥ ከመረጣቸው ይዞታዎች ውስጥ ግማሽ ያህሉ ብቁ አለመሆናቸው ተገለጸ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ ይዞታን...

ጉራጌን በክላስተር ለመጨፍለቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚቃወም ጎጎት ፓርቲ አስታወቀ

ለጉራጌ ሕዝብ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር እንደሚታገል የሚናገረው አዲሱ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...