Wednesday, March 29, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣን በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመመካከር በሚኒስትሩ ቢሮ ተገኝተው ውይይታቸውን ጀምረዋል]

  • ክቡር ሚኒስትር ባላንጣዎቻችን የእኛኑ ስልት መጠቀም የጀመሩ ይመስላል።
  • እንዴት? ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ?
  • እስከዛሬ እኛ የምንሰጣቸውን አጀንዳ ተቀባይ ነበሩ። በዚህም በውስጣቸው ልዩነትንና አለመግባባትን መትከል ችለን ነበር።
  • አሁን ምን ተፈጠረ?
  • ያልጠበቅነውን አጀንዳ ወደ እኛ ሜዳ ወርውረዋል።
  • ምን አደረጉ?
  • የድርቁን ጉዳይ ወርውረው አጋልጠውናል።
  • ታዲያ ምን ይሻላል ትላለህ?
  • ችግሩ በጣም አስከፊ ስለሆነ መፍጠን አለብን።
  • ምን ያህል አስከፊ ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ችግር ውስጥ ነው። በተለይ ደግሞ…
  • በተለይ ምን?
  • በተለይ በቦረና ዞን ያለው ሁኔታ አስከፊ ነው።
  • እንዴት?
  • በድርቁ ምክንያት ከ3.8 ሚሊዮን በላይ ከብቶች ሞተዋል።
  • ግን እኮ ድርቅ ከተከሰተ ከብቶች መሞታቸው አይቀርም።
  • ቢሆንም ክብር ሚኒስትር እነዚህ ከብቶች ለአርብቶ አደር ማኅበረሰባችን ህልውና መሠረት ናቸው።
  • እሱ መች ጠፋኝ?
  • ድርቁ አስከፊ መሆኑን እንዲገነዘቡ ብዬ ነው የችግሩን መጠን በአኃዝ ያቀረብኩት ክቡር ሚኒስትር።
  • ይገባኛል። እና ምን መደረግ አለበት ነው የምትለው?
  • ክቡር ሚኒስትር ሌሎች ፕሮጀክቶችን ለጊዜው ገታ አድርጎ በጀቱን በማዘዋወር ዜጎችን መታደግ አለብን።
  • ለጊዜው ገታ የምናደርገው ፕሮጀክት የለንማ። ሁሉም አስቸኳይና አንገብጋቢ ናቸው።
  • ለስድስት ወራት መዘግየት የሚችሉ አንድ ሁለት ፕሮጀክቶች አይጠፉም። እንደዚያ አድርገን የሰው ሕይወት ብንታደግ ይሻላል ክቡር ሚኒስትር።
  • የምናዘገየው ፕሮጀከት የለም እያልኩህ? እስኪ ንገረኝ የትኛው ፕሮጀክት ነው መዘግየት የሚችለው?
  • ለምሳሌ የቤተ መንግሥት ግንባታውን ለተወሰኑ ወራት ማዘግየት እንችላለን።
  • የትኛውን ቤተ መንግሥት?
  • አዲስ የሚገነባውን የጫካ ቤተ መንግሥት።
  • ቢቻል ጥሩ ነበር። ግን የሚሆን አይደለም።
  • ለምን?
  • የለውማ! አልተያዘለትም።
  • ምን?
  • በጀት!
  • እና በምን ገንዘብ ነው እየተገነባ ያለው?
  • ምርመራ እያደረክብኝ ነው?
  • ኧረ በጭራሽ ክቡር ሚኒስትር!?
  • ካልሆነ ኤምባሲዎቹ ጋብዘውሃል ማለት ነው።
  • ምን?
  • ዕራት!
  • በጭራሽ ክቡር ሚኒስትር። እንዴት በዚህ ይጠረጥሩኛል?
  • ምን ላድርግ ታዲያ?
  • እንዴት?
  • የማይነካ ነካሃ!
  • እኔማ መፍትሔ ይሆናል ብዬ አስቤ ነው። ታዲያ ምን እናድርግ ይላሉ ክብር ሚኒስትር?
  • አንድ መፍትሔ አለኝ።
  • ጥሩ። ምንድነው?
  • ባለሀብቶችን ማንቀሳቀስ አለብን።
  • የትኞቹን ባለሀብቶች?
  • አብረውን የሚሠሩ ባለሀብቶችን።
  • ጥሩ ሐሳብ ነው።
  • በተጨማሪም የተወረወረውን አጀንዳ በፍጥነት ማምከን አለባችሁ።
  • እንዴት አድርገን እናምክነው?
  • ሁሉም የመንግሥት ሚዲያዎች ስለድርቁ እንዲዘግቡ ይደረግ።
  • ምንም ነገር መደበቅ የለበትም?
  • መደበቅ አያዋጣም። ግን አንድ ነገር መዘንጋት የለበትም
  • ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • የሞተ ሰው የለም!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና የመንግሥት ውዝግብ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መንግሥት ባለፉት አራት ዓመታት...

በኦሮሚያ ክልል በስድስት ከተሞች የተዋቀረውን ሸገር ከተማን የማደራጀት ሥራ ተጀመረ

በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ስድስት ከተሞች የተዋቀረው ሸገር ከተማን...

 የክልሎች ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በመከላከያ ሠራዊት ተጠባባቂ ኃይል እንዲካተቱ ጥናት እየተደረገ ነው

የክልሎችን ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በአገር መከላከያ ሠራዊት ተጠባባቂ ኃይል...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...

አይ የእኛ ነገር!

የዛሬው ጉዞ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ነው፡፡ መንገዱ ለሥራ በሚጣደፉ፣...

የዓለም ኢኮኖሚ መናጋት ለወቅታዊው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ነው?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 16...

የተዘነጋው የከተሞች ሥራ የመፍጠር ተልዕኮ

በንጉሥ ወዳጅነው አሁን አሁን የአገራችን የሥራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ አንገብጋቢና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ አባላቱ የተከበሩ ተብለው የሚጠሩት በምክንያት አይደለም እንዴ? ትክክል ነው። ምክንያቱም፣ ምክር ቤቱ ትልቁ የሥልጣን አካል ነው፣...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...