- Advertisement -

ብልጽግና ፈተና ሆነውብኛል ያላቸውን አምስት ተግዳሮቶች ይፋ አድርጎ የአግዙኝ ጥሪ አቀረበ

ብልፅግና በነፃነት ስም በሚፈጸም ወንጀል ምክንያት በትግሉ ያገኘውን ነፃነት እያጣ መሆኑን አስታውቆ፣ ነፃነት ከኃላፊነት ጋር ሚዛናዊነቱን ጠብቆ እንዲሄድ የመንግሥት ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሚዲያዎች፣ የፍትሕ ተቋማት፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ምሁራንና የአገር ሽማግሌዎች የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ አስፈጻሚ ጥሪ አቀረበ፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከመጋቢት 7 እና 8 ቀን 2015 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ፣ ኢትዮጵያ ካለፈው መንገድ የመጣችበትን፣ ወደ ብልፅግና ለመሻገር በድልድዩ ላይ የቆየችበትን፣ በድልድዩ ላይ በቆየችባቸው ወቅቶች ያገጠሟትን ፈተናዎችና ተግዳሮቶች በዝርዝር መርምሮ፣ እያጋጠሙት ያሉ ፈተናዎች በዋናነት ከአምስት ነገሮች የመጡ መሆናቸውንና ለእነዚህም ተገቢ ነው ያለውን የትግል ስልት ቀይሷል፡፡ ታሪክ የሚመነጭ፣ ነፃነትን ለማስተዳደር አለመቻል፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን የሚፈታተኑ ሁኔታዎች እየገነገኑ መምጣታቸው፣ የኑሮ ውድነትና ሌብነት መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያውያን አያሌ አኩሪ ታሪኮችና በታሪክ ውስጥ ያገኘናቸው ዕድሎች ቢኖሩም፣ በተቃራኒው ደግሞ በታሪካችን ውስጥ ያልፈታናቸው፣ ተጨማሪ ችግር አድርገን የጨመርናቸውና ያልተግባባንባቸው ዕዳዎችም መኖራቸውን ጠቁሟል፡፡ ”እነዚህ ዕዳዎች የመነታረኪያ፣ የመጋጫና የመከፋፈያ ምክንያቶች ሊሆኑብን አይገባም፡፡ ዕዳዎቹን ወረስናቸው እንጂ አልፈጠርናቸውም፡፡ መጡብን እንጂ አልሄድንባቸውም” ብሏል፡፡

የተሻለው የመጀመሪያ መፍትሔ ለዕድሉም ለዕዳውም ተገቢውን ዕውቅና መስጠት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ዕድሉን ለመጠቀም፣ ዕዳውን ደግሞ ለማራገፍ ጠንክሮ መሥራት ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የሠለጠነና የሰከነ አካኼድ አዋጪ መሆኑን የዓለም ታሪክ አሳይቶናል፡፡ በመሆኑም ያለፉ ዕዳዎቻቸውን በሠለጠነና በሰከነ መንገድ በምክክርና በውይይት፣ በይቅርታና በዕርቅ ለመፍታት የሞከሩ አገሮች ግን ወደ ተሻለ መግባባትና ወደላቀ አንድነት ለመምጣት ችለዋል፡፡ እኛም የሚያዋጣን ይኼ ነው፡፡ የጀመርነው አገራዊ ምክክር እንዲሳካ እናድርግ ብሏል፡፡

- Advertisement -

ማዕከላዊ ኮሚቴው በመግለጫው እንዳብራራው፣ እንደ ውሻ አጥንት ከጠላት በሚወረወርልን አጀንዳ እየተራኮትን፣ ለልማት የምናውለውን ጉልበትና ጊዜ ለሤራ ትንተና እያባከንን፣ አንድ ጋት ወደ ብልፅግና ፈቀቅ ልንል አንችልም፡፡ አገር መውደድ ሌላውን ወገን በመውደድ እንጂ በመጥላት አይገለጽም፡፡ ለሌላው ወገን መስዋዕትነት በመክፈል እንጂ በግጭትና በትንኮሳ አይለካም፡፡ የሕዝብን ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ከሚንዱ፣ ጥላቻንና ግጭትን ከሚያባብሱ ንግግሮችና ድርጊቶች በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥትና የፓርቲ ኃላፊዎች ሊቆጠቡ እንደሚገባና የፓርቲና የመንግሥት አመራሮች ችግሮች በውይይትና በሕግ አግባብ ብቻ እንዲፈቱ ማድረግ እንዳለባቸው አብራርቷል፡፡

የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶች እንዲጠናከሩና መሠረት እንዲይዙ መሥራት አለባቸው፡፡ ሰላም እንዲሰፍን፣ ልማት እንዲጠናከር፣ ሕግና ሥርዓት እንዲከበር፣ መታገል በዋናነት ከአመራር የሚጠበቅ ሚና መሆኑን ለአፍታም ሊዘነጋ እንደማይገባና የሃይማኖት አባቶች፣ ሚዲያዎች፣ አክቲቪስቶችና ምሁራን ያለፉ ቁስሎችን ከሚቀሰቅሱ፣ ጥላቻን ከሚያነግሡ፣ ሕዝብ በጥርጣሬ እንዲተያይ ከሚያደርጉ፣ የሀገርን ሰላምና ደኅንነት አደጋ ላይ ከሚጥሉ ድርጊቶችና ንግግሮች እንዲጠበቁ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል፡፡

በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ባጋጠሙ ችግሮች የተነሳ በተፈጠረው የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት የኑሮ ውድነቱ እየጨመረ መምጣቱን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው መገምገሙን ጠቁሞ፣ ከኑሮ ውድነቱ ጋርም የሥራ አጥ መጠኑ መጨመሩን፣ ችግሩን በጊዜያዊነትና በዘላቂነት ለመፍታት ዕርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑንና ፈተናውን በብቃት ለመሻገር መንግሥት መራር ውሳኔ ሊወስንባቸው የሚገቡ ጉዳዮች መኖራቸውንም አረጋግጧል፡፡ ችግሩ በዘላቂነት እስከሚፈታ ድረስ መንግሥት የኑሮ ውድነቱን የሚያቃልሉ ጊዜያዊ ዕርምጃዎችን መውሰድ እንዳለበትና በችግሩ ላይ ቤንዚን የሚጨምሩ አካሄዶችን ማረም ተገቢ መሆኑን፣ ምርትን በተገቢ መጠን ለማምረትና ወደ ገበያ ለማድረስ የሚታዩ የአመራርና የአሠራር ችግሮች እንዳለባቸው አቅጣጫ አስቀምተጣል፡፡ በየአካባቢው የሚዘረጉ ኬላዎች ከሕግ አግባብ ውጭ የሚያካሂዱት ዕገዳና ዘረፋ በአመራር ቁርጠኝነትና ሕግን በማስከበር ሊፈታ ይገባዋል ብሏል፡፡

ብልፅግና ትልቅ ፈተና የሆነበት ሌብነት ሲሆን፣ አራት ኃይሎች የጋራ ግንባር ፈጥረው እየፈጸሙት መሆኑንና እነሱም በመንግሥት ውስጥ የሚገኙ ሌቦች፣ በባለሀብቱ አካባቢ ያሉ ሌቦች፣ በብሔር ዙሪያ ያሉ ሌቦችና በሚዲያው አካባቢ ያሉ ሌቦች እንደሆኑና ለአንድ ዓላማ አራት ሆነው እየሠሩ አገር እያጠፉ መሆናቸውን ኮሚቴው አብራርቷል፡፡ መንግሥት ሁሉንም ዓይነት ሌቦች ለማጥፋት የጀመረውን ዘመቻ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ ለዚህም የፓርቲው አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች እጃቸውን አስቀድመው ንጹሕ በማድረግ ትግሉን እንዲመሩ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ጥሪ አቅርቧል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን ሁሴን (አምባሳደር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት በሰላማዊ...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ሪፎርም በሦስት ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ሲሆን፣...

ጉራጌን በክላስተር ለመጨፍለቅ የሚደረገውን ጥረት እንደሚቃወም ጎጎት ፓርቲ አስታወቀ

ለጉራጌ ሕዝብ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበር እንደሚታገል የሚናገረው አዲሱ ጎጎት (ለጉራጌ አንድነትና ፍትሕ ፓርቲ) የጉራጌ ሕዝብን ክላስተር በሚባል ክልል አወቃቀር የመጨፍለቅ ጥረት እንደሚቃወም ተናገረ፡፡ ፓርቲው...

‹‹ኢኮኖሚው ላይ የሚታዩ ውጫዊ ጫናዎችን ለመቀልበስ የፖሊሲ ሪፎርሞች ያስፈልጋሉ›› ዓለም ባንክ

በዓለም ደረጃ ከተፈጠረው የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ጋር በተገናኘ፣ በኢትዮጵያ ውጫዊ የሆኑና ኢኮኖሚውን የሚገዳደሩ ጫናዎችን ለመፍታት፣ የማክሮ ፖሊሲ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ የዓለም ባንክ የምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ ምክትል...

ለአደጋ ሥጋት ተጋላጭ የሆኑ ተቋማትና ግለሰቦችን ለማስነሳት አስገዳጅ መመርያ ፀደቀ

በአበበ ፍቅር ለአደጋ ሥጋት ተጋላጭ የሆኑ ተቋማቶችንና ግለሰቦችን በሕጋዊ መንገድ ለማስነሳት የሚረዳ፣ አስገዳጅ መመርያ መፅደቁን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን...

አስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈጽሞባት ሕይወቷ ያለፈ ታዳጊን ታሳቢ ያደረገ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ

ከሳባት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ. በ2016 በ17 ዓመቷ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ሲፈጸምባት ሕይወቷ ባለፈው ‹‹ውብአንቺ›› የተባለች ታዳጊን ታሳቢ ያደረገ ፕሮጀክት በ206 ሚሊዮን ብር ይፋ ተደረገ፡፡ ወላጆችና...

አዳዲስ ጽሁፎች

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል ባንኮች ቁጥር ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ውስጥ ከዜሮ ተነስቶ ዛሬ ላይ 29 መድረሱ አንዱ ነው፡፡...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ ኃላፊነት ኃላፊነት ተሰጥቶት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን በመጀመሪያው ምዕራፍ ውጥኑ ሰባት ሺሕ ኪሎ ሜትር...

‹‹ልክ እንደ ሕክምና በፖለቲካውም ቅድመ ጥናት ተደርጎ ግጭቶችን መከላከል ያስፈልጋል›› ዶ/ር ተስፋዬ መኮንን፣ የሕክምና ባለሙያና ደራሲ

ዶ/ር ተስፋዬ መኮንን የተወለዱት በጅማ ከተማ ቢሆንም፣ ዕድገታቸውንና የልጅነት ጊዜያቸውን ያሳለፉት ሐረር ነው፡፡ ‹‹ወታደር አንድ ቦታ ስለማይቀመጥና የወታደር ልጅ በመሆኔ ዕትብቴ በተቀበረበት ጅማ ከተማ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን ሁሴን (አምባሳደር)፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሰሜን ኢትዮጵያን ጦርነት በሰላማዊ...

ብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን ይፋ ሊያደርግ ነው

የፋይናንስ ዘርፉን ለማረጋጋት የሚረዳ ሪፎርም ማጠናቀቁን የገለጸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡ አዲሱ የብሔራዊ ባንክ ሪፎርም በሦስት ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ሲሆን፣...

ግልጽነትና ተጠያቂነት የጎደለው አሠራር ለአገር አይበጅም!

ሰሞኑን የአሜሪካና የኢትዮጵያ መንግሥታት በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ተፈጽመዋል በተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና የጦር ወንጀሎች መግለጫ ላይ አልተግባቡም፡፡ አለመግባባታቸው የሚጠበቅ በመሆኑ ሊደንቅ አይገባም፡፡ ነገር ግን...

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን