Friday, June 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

  • አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር?
  • እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት?
  • እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ?
  • ምን?
  • እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል።
  • ይንገሩኝ ምንድነው ያሳሰበዎት?
  • ሌት ተቀን የሚሠራው ነጋዴ እየከሠረ ነው።
  • መቼም የውጭ ኃይሎች የፈጠሩብንን ችግር ያውቁታል።
  • ከእሱ አይገናኝም ክቡር ሚኒስትር!
  • እንዴት?
  • ሌት ተቀን የሚሠራ ታታሪ ነጋዴ ችግር እሱ አይደለም።
  • ምንድነው?
  • ታታሪ ነጋዴ እየመነመነ ሳለ በተቃራኒው ግን ሌላ…
  • በተቃራኒው ምን?
  • መሽቶ ሲነጋ ሀብት አፍርተው የሚታዩ ሰዎች እንደ አሸን እየፈሉ ነው።
  • ምን ማለትዎ ነው?
  • ጠንክሮ መሥራት ሀብት የሚፈጠርበት መንገድ መሆኑ ቀርቶ ሌላ ዓውድ ተፈጥሯል እያልኩ ነው።
  • የምን ዓውድ?
  • ሲነጋ ሀብታም መሆን የሚቻልበት ዓውድ።
  • አልገባኘም?
  • ምነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ምነው?
  • ሁሉን ነገር አስረዳ እያሉኝ እኮ ነው።
  • እውነት አልገባኝም? እንዴት ያለ ዓውድ ነው በብርሃን ፍጥነት ሀብት የሚያስገኘው?
  • አልገባኝም ካሉማ እንግርዎታለሁ።
  • ይንገሩኝ!
  • ሲነጋ ሀብት የሚፈጠርበት ስልት አንድና አንድ ነው።
  • ምንድነው?
  • ከከፍተኛ ባለሥልጣን ጋር ግንኙነት የመፍጠር ስልት ነው። ወንድም ወይም ዘመድ አዝማድ የመሆን ስልት!
  • እሱን ነው እንዴ?! ይህንንማ እኛም ገምግመናል።
  • ምን ብላችሁ ገመገማችሁት?
  • በዝተዋል ብለን ገምግመናል።
  • እነማን ናቸው የበዙት?
  • በብርሃን ፍጥነት ሀብታም እንሁን የሚሉ።

[የመደመር ትውልድ መጽሐፍን በመሸጥ ገቢውን ለታለመለት ፕሮጀክት ግንባታ እንዲያውሉ ለክልል ርዕሰ መስተዳድሮች ኃላፊነት እየተሰጠ ሳለ፣ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሲጠሩ የተሳቀበትን ምክንያት ለማወቅ የፈለጉት የሚኒስትሩ ባለቤት ሚኒስትሩን ለምን እንደተሳቀ እየጠየቁ ነው]

  • የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድርን ሲጠሩ ለምንድነው የተሳቀው?
  • አልሰማሽም እንዴ?
  • ምን?
  • ርዕሰ መስተዳድሩ መድረኩ ላይ ሲደርሱ የተናገሩት ያሉትን?
  • ምን አሉ?
  • ወደ ሚኒስትሩ ጠጋ ብለው ፕሮጀክቱን ጢያ ትክል ድንጋይ እናድርገው ሲሉ በድምጽ ማጉያው ውስጥ አልፎ ለታዳሚውም ተሰማ።
  • ታዲያ ይኼ ምን ያስቃል?
  • ያስቃል እንጂ።
  • ለምን?
  • የቀረው እሱ ነዋ!
  • ከምን?
  • ከደቡብ ክልል
  • እንዴት?
  • ሲዳማም ከደቡብ ክልል ወጥቶ ራሱን የቻለ ክልል ሆነ፡፡
  • እህ …
  • እነ ዳውሮም ራሳቸውን ችለው የደቡብ ምዕራብ ክልል ሆኑ።
  • እህ …ሰሞኑን ደግሞ …
  • ሰሞኑን ደግሞ ምን?
  • እነ ወላይታም የራሳቸውን ክልል ለመመሥረት ሕዝበ ውሳኔ ላይ ናቸው።
  • እህ… ልክ ነው ከደቡብ ክልል የቀሩት እነ ሶዶ ናቸው?
  • አዎ። ርዕሰ መስተዳድሩም ፕሮጀክቱን የጢያ ትክል ድንጋይ እናደርገው ያሉት ለዚያ ነው።
  • እህ… ሚኒስትሩ የተናገሩትም ምን ማለት እንደሆነ ገባኝ?
  • ምን ተናገሩ?
  • አልሰማህም እንዴ?
  • አልሰማሁም፣ ምን አሉ?
  • የመደመር ትውልድ ለደቡብ በጣም ያስፈልገዋል አሉ እኮ!
  • ምን ማለተቻው ነው? ምንድነው የገባሽ?
  • እኔን የገባኝ?
  • እ…?
  • ያው ሚኒስትሩ የገባቸው ነገር ነዋ።
  • ምንድነው እሱ?
  • ሚኒስትሩ የገባቸው?
  • እ…?
  • መደመር እያሉ ደቡብ ክልል መለያየቱ ነዋ።
  • አትሳሳቺ!
  • እንዴት?
  • በእርሳቸው መደመር ውስጥ መደመር ብቻ አይደለም ያለው።
  • ሌላ ምን አለ?
  • መቀነስ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን የሚተካ ረቂቅ ተዘጋጀ

ከቫት ነፃ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ገደብ ተቀመጠለት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሃያ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...