Tuesday, May 30, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊሕፃናትና አፍላ ወጣቶችን ከኤችአይቪ የመከላከሉ ሥራ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቆመ

ሕፃናትና አፍላ ወጣቶችን ከኤችአይቪ የመከላከሉ ሥራ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተጠቆመ

ቀን:

ባለፉት ዓመታት በተደረገው ርብርብ የኤችአይቪ ኤድስ ወረርሽኝን መቆጣጠር ቢቻልም፣ የሕፃናትና አፍላ ወጣቶች የኤችአይቪ መከላከል ምርመራና ሕክምና አገልግሎት ላይ ግን አሁንም ብዙ መሥራት እንደሚያስፈልግ፣ የጤና ሚኒስቴር አሳስቧል፡፡

የጤና ሚኒስቴር አዲስ በነደፈው አገር አቀፍ የሕፃናት ኤችአይቪ ፕሮግራም የማፋጠኛ ኢኒሽየቲቭ መሠረት፣ ኤችአይቪ ኤድስ ዳግም ወረርሽኝ እንዳይሆን እየተሠራ ነው፡፡

ሰሞኑን ኢንሽየቲቩ ሲገመገም የኤችአይቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ እንደገለጹት፣ ሕፃናትን ከኤችአይቪ የመከላከሉ ሥራ ላይ ክፍተት መኖሩን ተከትሎ፣ አገር አቀፍ የሕፃናት ኤችአይቪ ፕሮግራም የማፋጠኛ ኢንሽየቲቭ የታቀደ ሲሆን ፕሮግራሙም አበረታች ጅምር አሳይቷል፡፡

እንደ አቶ ፍቃዱ፣ ኤችአይቪ ኤድስ ተመልሶ ወረርሽኝ እንዳይሆንም በንቃት መከታተልና ኢኒሽየቲቩን በባለቤትነት ይዞ ተጠያቂነት ባለው አኳኋን መሥራት ያስፈልጋል።

ፕሮግራሙን በማስተዋወቅና ግንዛቤ ለመፍጠር፣ ጥራቱን የጠበቀ መረጃ ማደራጀት፣ የጤና ተቋማትን ማጠናከር ብሎም ቅንጅታዊ ሥራ መሥራት እንደሚያስፈልግም ሳይናገሩ አላለፉም።

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ እመቤት መኰንን በበኩላቸው፣ ራሱን ከኤችአይቪ የሚጠብቅ ትውልድ ለማስረከብ ትውልዱ ላይ መሥራት እንደሚጠበቅ፣ ይህን ለማስፈጸምም ሕፃናትን የመመርመር ሥራ ትልቅ የትኩረት አቅጣጫ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

የኢንሽየቲቩ አጋር ድርጅቶች፣ ባለፉት ዓመታት በጤና ሚኒስቴር አመራር ሰጪነት፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የኤችአይቪ ሥርጭትን ለመቆጣጠር በጋራ እየሠሩ መሆኑን በዚህም በርካቶችን መታደግና አዳዲስ የኤችአይቪ ኢንፌክሽኖችን መቀነስ መቻሉን ገልጸዋል።

በኤችአይቪ ፕሮግራም እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶች እጅግ በጣም ብዙ ቢሆኑም፣ ሕፃናትና ወጣቶች ላይ ያነጣጠሩ አገልግሎቶችን ማሳደግ የረዥም ጊዜ ፈተና ሆኖ መቆየቱንም ጠቁመዋል።

ከኤችአይቪ ጋር የሚኖሩ ሕፃናትና ጎረምሶች ጉዳይን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የኢንሽየቲቩ አጋር ድርጅቶች መገለጻቸውንም ሚኒስቴሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...