Thursday, June 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ከተቃዋሚ ፓርቲው ትይዩ ሚኒስትር ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ እየተወያዩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ ላይ ፓርቲያችን ማጣራትና ማረጋገጥ የሚፈልጋቸው ጉዳዮች በመኖራቸው ነው እርስዎን ለማግኘት የጠየቅሁት።
  • ሌሎች ፓርቲዎችም የእናንተን መንገድ ቢከተሉ ጥሩ ነበር።
  • እንዴት?
  • ምክንያቱም አበክረው ሲጠይቁት ለነበረው ጥያቄ መንግሥት ምላሽ ሲሰጥ ጾመኞች ነን አሉ።
  • ክቡር ሚኒስትር እኛም ለመለየት ተቸግረናል።
  • ምኑን?
  • የትኛው የፍስክ፣ የትኛው ደግሞ የጾም እንደሆነ።
  • ለምን?
  • ምክንያቱም አንዳንድ አመራሮች መንግሥት ልዩ ኃይልን የማፍረስም ሆነ የመበተን ፍላጎት የለውም ይላሉ።
  • እውነት ነው።
  • ሌሎች አመራሮች ደግሞ በመንግሥት ውሳኔ መሠረት የክልል ልዩ ኃይሎች ወደ መከላከያ እንደሚቀላቀሉ ይገልጻሉ።
  • ልክ ነው!
  • የቱ ነው ልክ?
  • ሁለቱም፡፡
  • የክልል ልዩ ኃይል አይፈርስም?
  • እኛ ልዩ ኃይልን የማፍረስ ዕቅድ ጨርሶ የለንም። መልሶ የማደራጀት ውሳኔ ነው ያሳለፍነው፡፡
  • ስለዚህ ወደ መከላከያ ይቀላቀላል የሚባለው ትክልል አይደለም?
  • ትክልል ነው እንጂ! ይቀላቀላሉ።
  • ካልፈረሱ እንዴት ሆነው ወደ መከላከያ የሚቀላቀሉት?
  • ምን ችግር አለው? ቀላል እኮ ነው።
  • በምን ዓይነት አደረጃጀት ሊቀላቀሉ ይችላሉ?
  • ማለት?
  • ከተቀላቀሉ በኋላ በመከላከያ ሠራዊት የአማራ ልዩ ኃይል ወይም የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ነው አደረጃጀታቸው?
  • እርስዎም እንደ ሌሎቹ ተቃዋሚዎች ከሥጋው እጾማለሁ ሊሉ ነው?
  • አይደለም፣ ተሳስተዋል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • እርስዎ ነዎት የተሳሳቱት፡፡
  • እንዴት?
  • ምክንያቱም የጠቀሱት አደረጃጀት በሙከራ ጭምር የሚያስጠይቅ ነው።
  • የምን ሙከራ?
  • ሕገ መንግሥቱን በኃይል የመናድ፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር እንዴት እንደዚህ ይላሉ?
  • በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ የሌለ የክልል ልዩ ኃይል አደረጃጀትን ማንሳት ሕግ መንግሥቱን የመናድ ዕሳቤ ቅጥያ ነው!
  • ክቡር ሚኒስትር ከእርስዎ ማብራሪያ ተነስቼ ያልኩት ነው?
  • እኔ እንደዚያ ወጣኝ?
  • መንግሥት የክልል ልዩ ኃይልን የማፍረስ ዕቅድ የለውም ነገር ግን ወደ መከላከያና ሌሎች የፌዴራል የፀጥታ ተቋማት ይቀላቀላሉ አላሉም?
  • ብያለሁ፡፡
  • ታዲያ?
  • እስኪቀላቀሉ ድረስ ነዋ!
  • እንደዚያ ከሆነ ያድርጉልኝ?
  • ከምኑ?
  • ከሥጋውም ከመረቁ!

[የጊዜያዊ አስተዳደሩ መሪ ወደ ሚኒስትሩ ደውለው መንግሥት ሰሞኑን ባወጣው መግለጫ ላይ ማብራሪያ እየጠየቁ ነው]

  • ክብርት ሚኒስትር፣ ሰላም?
  • ሰላም ነኝ፣ ምን እግር ጣለዎት?
  • ምን ስልስ ጣለዎት ነው የሚባለው።
  • ኪኪኪኪ … እውነት ነው። እንዲህ ስንደዋወል ደስ ይላል። ምን ጉዳይ ገጠመዎት?
  • መቼም አንዳንዴ ግርታ አይጠፉም ወይም ያንን ስልት እኛ ላይም መጠቀም ጀምራችሁ ይሆናል።
  • የቱን ስልት?
  • ኮንፊውዝና ኮንቪንስን፡፡
  • እንዴት?
  • መንግሥት ሰሞኑን የሰጠው መግለጫ ግራ አጋብቶናል።
  • ለምን?
  • ክቡር ሚኒስትር በግልፅ እንደሚረዱት የመከላከያ ሠራዊት አካል ያልሆኑ የፀጥታ ኃይሎች ከትግራይ ክልል እንደሚወጡ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ማስፈጸሚያ ተስማምተናል።
  • አዎ። ትክክል ነው።
  • በፕሪቶሪያው ስምምነት ላይ የሰላም ስምምነቱ ዓላማ ተብለው የተዘረዘሩት ነጥቦች አንዱም በቀጥታ ከዚህ ጋር እንደሚገናኝ የሚገነዘቡ ይመስለኛል።
  • ልክ ነው። እስኪ ያስታውሱኝ፣ የትኛው ነጥብ ነበር?
  • በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ክልል የተስተጓጎለውን ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ወደነበረበት መመለስ አንደኛው የስምምነቱ ዓላማ ነው።
  • አዎ። አስታወስኩት። ትክክል ነው።
  • መንግሥት ሰሞኑን የሰጠው መግለጫ ግን ይህንን ያላገናዘበ ይመስላል። በእኛ ላይም ግራ መጋባትን ፈጥሯል።
  • የትኛው መግለጫ ነው?
  • የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ የተሰጠው።
  • ይህ መግለጫ ደግሞ እናንተ ላይ እንዴት ግርታ ይፈጥራል?
  • ፈጥሯል!
  • እኮ እንዴት?
  • ምክንያቱም የክልል ልዩ ኃይሎችን በተመለከተ መንግሥት ያሳለፈው ውሳኔ ከፕሪቶሪያው ስምምነት ጋር አይገናኝም ይላል።
  • ልክ ነው ይላል።
  • እርስዎም ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ የመንግሥት ውሳኔ ከሰላም ስምምነቱ ጋር አይገናኝም ብለው ቃል በቃል ደግመውታል።
  • አይገናኝም ብቻ አይደለም ያልኩት፡፡
  • እ…?
  • ከሰላም ስምምነቱም አይጣረስም ብያለሁ!
  • እንደዚያ ማለትዎን አልሰማሁም።
  • እንደዚያ ነው ያልኩት።
  • ከሆነማ መግለጫውም እንደ እርስዎ ነው።
  • እንደ እርስዎ ማለት?
  • ሰላማዊ ነው።
  • ነገር ግን ስምምነቱን ለማስፈጸም ብለን የወሰነው አይደለም።
  • ለምንድነው?
  • የአገራዊ ዕቅዳችን አካል ስለሆነ ነው።
  • ቢሆንም …ክቡር ሚኒስትር ቢሆንም?
  • ቢሆንም ምን?
  • ሚዛናዊ ነው!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

‹‹ወልቃይት የአማራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያም እስትንፋስ ነው›› አቶ ዓብዩ በለው፣ የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት

ለወልቃይት የአማራ ማንነት መከበር የሚታገለው የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት...

በተቃርኖዎች መሀል የሚዋልለው የብልፅግና መንግሥት

ርዕዮተ ዓለም እንኳ የሌለው ይሉታል የሚቃወሙት ወገኖች፡፡ እሱ ግን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...