Thursday, June 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[የክቡር ሚኒስትሩ ባለቤት የቴሌቪዥን ቻናሎችን እየቀያየሩ ሲመለከቱ ቆይተው አንድ ጉዳይ ቀልባቸውን ስቦ ጥያቄ ሰነዘሩ]

  • የሱዳን የጦር ኃይሎች በከተማ ውስጥ እርስ በርስ ፍልሚያ መጀመራቸውን ሰማህ?
  • አዎ። ወንድም የሆነውን ሕዝብ ለመከራ ዳረጉት።
  • እኔ እንኳን እሱን ለማለት አልነበረም።
  • እና ምን ልትይ ነበር?
  • ነገሩ ከሰሞኑ ውሳኔያችሁ ጋር መገጣጠሙ ገርሞኝ ነው።
  • የቱ ውሳኔ?
  • የክልል ልዩ ኃይሎችን አስመልክቶ የወሰናችሁት።
  • ምን አገናኘው?
  • የሱዳኑ ክስተት እናንተ ካስረዳችሁት በተሻለ ሁኔታ ስለ ውሳኔያችሁ ምክንያትና አስፈላጊነት ግንዛቤ ይፈጥራል ማለቴ ነው።
  • እንዴት? የእኛ ምክንያት ምንድነው?
  • ፍርኃት ነዋ!
  • የምን ፍርኃት?
  • የሱዳኑ እንዳይከሰት።
  • ፍርኃት እንኳን አይደለም። ቢሆንም ሌላውም በዚህ መልኩ ቢረዳው ጥሩ ነበር።
  • ምን ያድርጉ ብለህ ነው?
  • እንዴት?
  • እነሱም ፈርተው ነዋ።
  • ለምን ይፈራሉ?
  • ሌላ ኃይል ይወረኛል፣ መሬቴን ይወስዳል ብለው ይሆናላ።
  • እነሱ እንኳ ገና ከግጭት እየወጣን ስለሆነ ቢሰጉ አይገርምም፣ የሕዝቡ ግን ግራ ያጋባል።
  • የሕዝቡ ምን?
  • ለተቃውሞ አደባባይ ወጥቶ መንገድ መዝጋቱ?
  • ምን ያድርግ ብለህ ነው?
  • እንዴት?
  • ፈርቶ ነዋ!
  • ለምን ይፈራል?
  • ያፈናቅሉኛል፣ ጥቃት ይደርስበኛል ብሎ ነዋ?
  • መንግሥት ባለበት አገር?
  • መንግሥት ያነጻጽር ይሆናል እንጂ አይጠብቀኝም ብሎ ይሆናላ?
  • የምን ንጽጽር? ከምን?
  • አሜሪካ ላይ ከደረሰ ጥቃት፡፡
  • ካንቺ ቁም ነገር መጠበቄ ነው ስህተቱ፡፡
  • አትሳሳት! ቁም ነገር ነው ያወራሁት!
  • ምኑ ነው ቁም ነገሩ?
  • የዚህ አገር ችግር ምን እንደሆነ እየነገርኩህ እኮ ነው?
  • ምንድነው የዚህ አገር ችግር?
  • ፍርኃት!
  • የምን ፍርኃት?
  • አለመተማመን የወለደው ፍርኃት፡፡

[ክቡር ሚኒስትሩ ዋና ጸሐፊው ጉብኝት እንዳያደርጉ መከልከላቸውን በተመለከተ ስለወጣው መረጃ ከአማካሪያቸው ጋር እየተወያዩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር ባዘዙኝ መሠረት ዋና ጸሐፊው ጉብኝት እንዳያደርጉ የከለከለው ማን እንደሆነ የሚመለከታቸውን ተቋማት መረጃ ጠይቄያለሁ።
  • እሺ፣ ምን ምላሽ አገኘህ?
  • አንዳንዶቹ ጨርሶ መረጃውን አልሰሙም።
  • እነሱን ተዋቸውና የሌላውን ንገረኝ።
  • የውጭ ግንኙነት ሰዎች በዚህ ጉዳይ ኦፊሳላዊ ምላሽ እንደማይሰጥ ነው የነገሩኝ።
  • እንዴ? አጋሮቻችን ኦኮ እየጠየቁን ነው? ምላሽ የለንም ልንላቸው ነው?
  • እኔም ይህንኑ ጥያቄ አንስቼ ነበር።
  • እሺ ምን አሉህ?
  • የግድ ምላሽ ለሚፈልጉት ብቻ ማለት ያለብንን ነግረውኛል።
  • ምን በሏቸው አሉ?
  • እኛ አልከለከልንም፣ የመንግሥት አቋም አይደለም!
  • ምን ማለት ነው? ማነው የወሰነው ብለው መጠየቃቸው ይቀራል እንዴ?
  • አኔም ይህንኑ አንስቼ ነበር።
  • እሺ፣ ማን አሉ?
  • በግላቸው!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ሥጋቶች

ዘ ኮንቨርሴሽን ላይ ‹‹What Next for Ethiopia and its...

‹‹ወልቃይት የአማራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያም እስትንፋስ ነው›› አቶ ዓብዩ በለው፣ የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት

ለወልቃይት የአማራ ማንነት መከበር የሚታገለው የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...