Thursday, June 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአማካሪያቸው ጋር ሰላምን ስለማፅናትና ስለ ሰላም ድርድር እየተወያዩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር ስለ ሁለተኛው ዙር ድርድር የሚያውቁት ነገር አለ?
  • ሁለተኛ ዙር ድርድር ማለት?
  • ሰሞኑን ይጀመራል ስለተባለው?
  • ‹‹ጦርነት ይብቃ፣ ሰላምን እናፅና›› ብለን ሰሞኑን ዕውቅና ሰጥተን ጉዳዩን ዘግተነው የለም እንዴ?
  • እሱንማ አውቃለሁ።
  • ታዲያ ሁለተኛ ዙር የሰላም ድርድር የምትለው ምንድነው?
  • በታንዛኒያ የሚካሄደውን ማለቴ ነው?
  • እ … እሱን ነው እንዴ?
  • አዎ።
  • ታዲያ ምን ማወቅ ፈልገህ ነው?
  • ሸኔ የሚባለው ማን እንደሆነ ማወቅ ፈልጌ ነው?
  • ምን ማለትህ ነው? የትጥቅ ትግል የከፈተብን ነዋ?
  • የት?
  • እዚሁ አገራችን ውስጥ ነዋ?
  • አገር ውስጥ መሆኑማ ገብቶኛል። የትኛው እንደሆነ ግን ለማወቅ አልቻልኩም።
  • እንዴት? ስንት ሸኔ አለና ነው ለማወቅ የተቸገርከው?
  • ባለፈው በሁለት አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ሸኔዎች እንዳሉ አለቃ ሲናገሩ አልነበረ እንዴ?
  • እህ … እሱ ነው ግራ ያጋባህ?
  • አዎ።
  • እንዲያው ዝም ብለህ እንጂ ነገሩ እንኳን ግራ የሚያጋባ አልነበረም።
  • እንዴት ክቡር ሚኒስትር?
  • ገና ለድርድር አልደረሰማ!
  • ምኑ?
  • አንደኛው ሸኔ።
  • ታዲያ ከየትኛው ጋር ነው ድርድሩ የተጀመረው?
  • በሌላ ክልል ከሚንቀሳቀሰው ጋር።
  • ከእሱኛው ሸኔ ነው?
  • አዎ። ምነው ደነገጥክ?
  • እንዴት ከዚህ ቡድን ጋር መንግሥት ለሰላም ድርድር ተቀመጠ ብዬ ነዋ?
  • ይህማ መንግሥታችን የሚገለጽበት አንዱ ባህሪ ነው።
  • የቱ?
  • ሆደ ሰፊነቱ!
  • ግን ክቡር ሚኒስትር ቡድኑ የሚያነሳው ጥያቄ በሰላም ድርድር የሚፈታ ነው?
  • እንዴት?
  • ምክንያቱም ቡድኑ ወደ ትጥቅ ትግል የገባበት ዓላማ ይታወቃል። አሁንም ይህንኑ ዓላማውን ከማሳካት ወደ ኋላ እንደማይመለስ በይፋ እየገለጸ እኮ ነው?
  • የትግሉ ዓላማ ምንድነው?
  • እሱማ ግልጽ አይደል እንዴ?
  • እኮ ለእኔ ግልጽ አድርግልኛ?
  • እንዴ ክቡር ሚኒስትር?
  • አቤት? ግልጽ አድርግልኛ?
  • እኔ ግልጽ ነው አልኩኝ እንጂ፣ ሌላ ነገር እኮ አልተናገርኩም?
  • ሌላ ነገር ምን?
  • የትግል ዓላማው ትክክል አይደለም አላልኩም።
  • አዎ፣ እንደዚያ አላልክም።
  • ትችትም አልሰነዘርኩም።
  • አዎ፣ አልተቸህም።
  • እደግፋለሁም አላልኩም።
  • ምን ሆንክ? ጤነኛ አይደለህም እንዴ?
  • ኧረ ደህና ነኝ ክቡር ሚኒስትር።
  • ታዲያ ለምን ተደነባበርክ፣ የትግል ዓላማውን ግለጽልኝ ነው እኮ ያልኩህ?
  • እሱንማ ሰምቻለሁ።
  • እኮ ግለጽልኛ?
  • የክልሉ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን መብት እስኪያገኝ ድረስ እታገላለሁ ነው የሚለው።
  • እርግጠኛ ነህ?
  • አዎ! በድረገጹ ላይም ሆነ በሚዲያዎች በይፋ ነው የሚገለጸው።
  • አልቀየረም?
  • አልቀየረም። ይህንን ማሳካት ነው የሚፈልገው።
  • እንዴት? ይህማ አይሆንም!
  • እኔም የሰላም ድርድር ሊጀመር ነው ሲባል ግራ የገባኝ በዚህ ምክንያት ነው።
  • እንደዚያማ ሊሆን አይችልም።
  • እንዴት?
  • የሰላም ሊባል አይችልም።
  • ምኑ?
  • ድርድሩ።
  • ታዲያ የምን ሊባል ነው።
  • ድርድር።
  • እኮ የምን ድርድር ሊባል ይችላል?
  • ድርድር ብቻ!
  • ምን ለማሳካት?
  • እሱን አብረን እንሰማለን።
  • መቼ?
  • መጨረሻ ላይ።

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ሥጋቶች

ዘ ኮንቨርሴሽን ላይ ‹‹What Next for Ethiopia and its...

‹‹ወልቃይት የአማራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያም እስትንፋስ ነው›› አቶ ዓብዩ በለው፣ የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት

ለወልቃይት የአማራ ማንነት መከበር የሚታገለው የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...