Thursday, June 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[የተጠናቀቀውን ሪዞርት ለመመረቅ የተሳፈሩትን ሚኒስትሮችና የክልል ፕሬዚዳንቶች የያዘው አውሮፕላን ወደ ማረፊያው መቃረቡን የተመለከቱት የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት፣ የት አካባቢ እንዳሉ ግራ ገብቷቸው አጠገባቸው የተቀመጡትን ሚኒስትር እየጠየቁ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር ምንድነው ነገሩ?
  • ምኑ?
  • ምዕራብን እንጎበኛለን አይደል እንዴ የተባለው?
  • አዎ ደርሰናል፣ ለማረፍ እየተቃረብን ነው።
  • ይኼ ባለፈው የመጣንበት አካባቢ አይደል እንዴ?
  • አዎ፣ ልክ ነዎት።
  • እኔ እኮ ወደ ምዕራብ መስሎኝ ነው ተጣድፌ የመጣሁት።
  • የትኛው ምዕራብ?
  • የእኛ ምዕራብ።
  • አይቀልዱ እንጂ ክቡር ፕሬዚዳንት?
  • እንዴት?
  • አገሪቱ እኮ ወደ ላይ አይደለም የቆመችው?
  • ምን ማለትዎ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • የእናንተ አካባቢ ብቻ ሳይሆን፣ አገሪቱም አላት ማለቴ ነው።
  • ምን?
  • ምዕራብ!
  • ቢሆንም ሪዞርት ልንመርቅ ነው ተብዬ ብጠራ ይሻል ነበር።
  • ለማንኛውም ደርሰናል፣ እየወረዱ።
  • ይቅደሙ ክቡር ሚኒስትር፣ የእርስዎ ፕሮጀክት አይደል ይቅደሙ።
  • እሺ… እንዴት አገኙት ታዲያ?
  • እኔማ ያኔ የሰላሙን ሁኔታ ለመገምገም ስመጣ ያለቀ ነበር የመሰለኝ።
  • ከዚያ በኋላ ብዙ ነገሮች ተሠርተዋል፣ ለምሳሌ እዚያ ጋ ያለውን ይመልከቱ… ያኔ አልነበረም።
  • አዎ፣ በጣም አረንጓዴ ሆኗል።
  • አረንጓዴ መሆኑን ብቻ ነው ያስተዋሉት?
  • እሱማ ማለቅ የነበረባቸው ነገሮችም አልቀዋል… በተጨማሪም
  • እ…
  • በተጨማሪ ምን?
  • መከርከም የነበረባቸውም ተከርክመዋል፡፡
  • አሁን አንድ ነገር ብቻ ነው የሚቀረን።
  • ምንድነው እሱ?
  • ማን ያስተዳድረው የሚለውን ገና አልወሰንም።
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • አስተዳደሩን ለማን እንስጥ የሚለውን ገና እየተወያየንበት ነው።
  • ማን ያስተዳድረው የሚለውማ ተወስኗል፣ በግልጽ ተቀምጧል እኮ ክቡር ሚኒስትር?
  • ማነው የወሰነው? ምኑ ላይ?
  • ስምምነቱ ላይ፡፡
  • ስለምንድነው እርስዎ የሚያወሩት? አሁንም እዚያው ነዎት እንዴ?
  • የት?
  • ለማንኛውም ወደ እዚህኛው ቢመለሱ ይሻላል፡፡
  • ወደ እዚህኛው ምን?
  • ምዕራብ!

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ስለተከሰሱ ሰዎች የሚተላለፈውን ዜና በተመስጦ እየተከታተሉ አገኟቸው]

  • ምንድነው እንዲህ ተመስጠሽ የምታደምጪው?
  • ሰበር ዜና ነው።
  • ስለምንድነው?
  • በሽብርተኝነትና የክልሉን መንግሥት በኃይል ለመጣል ተጠረጥረው ስለተያዙና ስለሚፈለጉ ሰዎች ነው።
  • እ… ስለእሱ ነው።
  • አዎ፣ ታውቅ ነበር እንዴ?
  • እንኳን እኔ እነሱ ራሳቸው የሚያውቁ አይመስለኝም።
  • ይደንቃል፡፡
  • በአሸባሪነት መጠርጠር የለባቸውም ብለሽ ልትሟገቺ ነው?
  • እኔ ምኑን አውቄ እሟገታለሁ?
  • ታዲያ ምንድነው ያስደነቀሽ?
  • ገና ሲጀመር አዲስ አበባ አካባቢ ያሉ ሰዎች ነበሩ በሽብርተኝነት የተከሰሱት።
  • እሺ?
  • ከዚያ ወደ ሰሜን ሄደ።
  • ወደ ሰሜን ማለት?
  • የመጀመሪያው ከሳሽ የነበሩት ራሳቸው ሽብርተኛ ተብለው አልነበር?
  • አዎ፣ ለካ እነሱም አልቀረላቸውም።
  • አሁን ደግሞ ሌላኛው ሰሜን ተረኛ ይመስላል።
  • ካልሽማ ወደ ምዕራብም ዘልቆ ነበር።
  • ይህ እኮ ነው ድንቅ የሚለኝ።
  • ምኑ?
  • የሚንሸራሸረው፣ ማለቴ የሚሽከረከረው ነገር?
  • ምኑ?
  • የሽብርተኝነት ክሱ ነዋ?
  • እንዴት?
  • እንደምን ልበልህ፣ አዎ… እንደ እንትን… ስሙ ምን ነበር?
  • እንደምን?
  • የብሔር ብሔረሰቦች ዋንጫ፡፡
  • ኪኪኪ… ወደው አይስቁ አሉ፣ ታሾፊያለሽ አይደል?
  • እያሾፍኩ አይደለም።
  • ታዲያ ምን እያደረግሽ ነው?
  • ከምሬ ነው፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እዚህ አገር የሚሽከረከሩ ነገሮች እየበዙ እያየሁ እገረማለሁ።
  • ሌላ ምን ተሽከረከረ ልትይ ነው ደግሞ?
  • አንዱ እንዳልኩህ ዋንጫው ነው።
  • እሺ ሁለተኛ የሽብርተኝነት ክስ ያልሽው መሆኑ ነው?
  • አዎ፣ ሌላው ደግሞ ግጭትና የጦር መሣሪያ ነው።
  • እሺ ሌላውስ?
  • ሌላው ደግሞ ኮማንድ ፖስት ነው።
  • ኪኪኪኪ… እሺ ሌላ የሚደንቅሽ ነገር የለም?
  • የሚደንቅ ነገር አይጠፋም።
  • ለምሳሌ ምን?
  • ሽብርተኛ የተባሉት ሰዎች በመጨረሻ ላይ የሚሆኑት ነገር።
  • ምን ይሆናሉ?
  • የካቢኔ አባል!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

‹‹ወልቃይት የአማራ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያም እስትንፋስ ነው›› አቶ ዓብዩ በለው፣ የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት

ለወልቃይት የአማራ ማንነት መከበር የሚታገለው የልሳነ ግፉአን ድርጅት ፕሬዚዳንት...

በተቃርኖዎች መሀል የሚዋልለው የብልፅግና መንግሥት

ርዕዮተ ዓለም እንኳ የሌለው ይሉታል የሚቃወሙት ወገኖች፡፡ እሱ ግን...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...