Friday, June 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ክፍያ መንገድ ብቻ እንዲፈጸም የተላለፈውን ውሳኔ አተገባበር ላይ ስለተነሱ ቅሬታዎች ከባልደረባቸው ጋር እየተወያዩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር አተገባበሩ ጥሩ ቢሆንም፣ ከፍተኛ ወቀሳ እየደረሰብን ነው።
  • ዲጂታል የግብይት ሥርዓቱን ለማስፋፋት በመጣራችን መመስገን ሲገባን እንዴት እንወቀሳለን?
  • የሚገርመው በዲጂታል ክፍያ ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች ናቸው በዋነኛነት እየወቀሱን ያሉት።
  • ለምን?
  • እኛም የዲጂታል ክፍያ አገልግሎት ብንሰጥም፣ አንድ ተቋም ብቻ በአድሎ ገበያውን እንዲቆጣጠርና ከጫወታ ውጪ እንድንሆን ተገፍተናል እያሉ እየወቀሱን ነው።
  • ይህ ተቋም የተመረጠው የተሻለ ልምድና ተደራሽነት ስላለው ነው ብላችሁ በበቂ ሁኔታ አላስረዳችሁም ማለት ነው?
  • ኧረ አስረድተናል ክቡር ሚኒስትር።
  • ታዲያ ለምን ወቀሳ መጣብን?
  • ማኅብረሰቡ ልምድ የላችሁም፣ ተደራሽ አይደላችሁም ብሎ የፈለገውን ይምረጥ እንጂ መንግሥት እንዴት ይወስናል ነው የሚሉት።
  • መንግሥት ለማኅበረሰቡ ምቹ ሁኔታ የመፍጠር ግዴታ እንዳለበትማ መዘንጋት የለበትም።
  • እኛም ይህንኑ አስረድተናል ነገር ግን የመንግሥትና የግል ባንኮች እንዲሁም አዲስ የገባው የውጭ ቴሌኮም ሳይቀር ውሳኔውን ተቃውመውታል። እንዲያውም አንዳንዶቹ …
  • እ … አንዳንዶቹ ምን?
  • ብዙ ተከታይ ያላቸው የማኅበራዊ ሚዲያ ተዋናዮችን በማሰማራት እየተሳለቁብን ነው።
  • ምን እያሉ ነው የሚሳለቁት?
  • የቀጣዩ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥም በዚሁ ነው እያሉ።
  • የማይሆን ነገር ነው የሚያወሩት!
  • ሌላም ብዙ ተሳልቀዋል።
  • ምን አሉ?
  • ነገሩ በዚሁ ከቀጠለ ቤንዚን የሚስቡ የጎዳና ልጆችንም ተጠቀሙ መባለቸው አይቀርም ሲሉም ተሳልቀዋል።
  • ምን?
  • ቴሌ ብር!
  • በሉ ይሄንን ነገር በፍጥነት ተቆጣጠሩ።
  • እንዴት አድርገን?
  • ሁሉም ንግድ ባንኮች በግብይቱ እንዲሳተፉ ይደረግ።

[የክቡር ሚኒስትሩ አማካሪ ሰሞኑን የተላለፈው መልዕክት ማንን እንደሚመለከት ሚኒስትሩን እየጠየቀ ነው]

  • የትኛውን መልዕክት ነው የምትለው?
  • ደቡብ ምዕራብ ላይ የተገነባው ሪዞርት ሲመረቅ የተላለፈውን ማለቴ ነው። እርስዎም እኮ ቦታው ላይ ነበሩ?
  • አዎ። ተገኝቼ ነበር፣ ግን የተላለፈውን መልዕክት ዘነጋሁት፣ ምን ነበር?
  • ‹‹በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ገብታችሁ የምትፈተፍቱ የውጭ ኃይሎች፣ የእኛን ጉዳይ ለእኛ ተውሉን›› የተባለውን ማለቴ ነው።
  • እ … አስታወስኩት። ልክ ነው ማቆም አለባቸው!
  • ግን የውጭ ኃይሎች የተባሉት እነማን ናቸው?
  • በአጠቃላይ የውጭ ኃይሎችን የሚመለከት ነው።
  • ጎረቤት አገርን ይሆን እንዴ?
  • ለምን ጎረቤት ጠረጠርክ?
  • መልዕክቱ ላይ ጎረቤት አገር ልትሆን እንደምትችል የሚጠቁም ነገር የሰማሁ ይመስለኛል።
  • ምን የሚል?
  • ብዙ ያልሠራችሁት ነገር ስላለ የእኛን ጉዳይ ለእኛ ተውሉንና በምድራችሁ ያልሠራችሁትን ሥሩ የሚል መልዕክት አብሮ ተላልፏል።
  • ታዲያ ይኼ ጎረቤት አገር መሆኑን ይጠቁማል እንዴ?
  • መቼም ኃያሏን አገር ሊሆን አይችልም ብዬ ነው። በዚያ ላይ …
  • በዚያ ላይ ምን?
  • በዚያ ላይ የታሰበው ሳይለቀቅ አይናገሯትም ብዬ አስቤ ነው።
  • ለማንኛውም መልዕክቱ ጎረቤት አገርንም ሆነ ኃያሏን አገር በስም አልጠቀሰም።
  • ምን አልባት እርሶ የሚያውቁ ከሆነ ብዬ እንጂ በስምማ አልተጠቀሰም።
  • መልዕክቱ ሁሉንም የውጭ ኃይሎች የሚመለከት ነው።
  • እንዴት ሁሉንም ሊሆን ይችላል ክቡር ሚኒስትር? ቢያንስ በውስጥ ጉዳይ የሚፈተፍቱ መሆን አለባቸው።
  • እኮ እንደዚያ የሚያደርጉትን ሁሉንም ማለቴ ነው።
  • ግን ጎረቤት አገር እንደምትሆን ይሰማኛል።
  • እንዴት? በምን ምክንያት?
  • ምክንያቱም ቅድም ከጠቀስኩት ውጤት ሌላ ጠቋሚ ነገር ያለ ይመስለኛል።
  • ምን?
  • የውጭ ኃይሎችና በተለይ ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ኃይሎች የሚል ጠቋሚ ነገርም በመልዕክቱ ተላልፏል።
  • ታዲያ ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ የሚለው ምን ይጠቁማል?
  • መረጃ እየተቀበሉ የሚጽፉትን ትውልደ ኢትዮጵያዊ ለማለት ፈልገው ይመስለኛል።
  • መረጃ የሚቀበሉት ከማን ነው?
  • ከጎረቤት አገር መረጃና ደኅንነት ይመስለኛል።
  • እኔ ግን እሳቸውን ለማለት የፈለጉ አይመስለኝም።
  • ታዲያ ረሺድ አብዲ ነው ሊሉኝ ነው።
  • እሱማ እዚህ መጥቷል?
  • የት? አዲስ አበባ?
  • አዎ!
  • በኢንተር ፖል ነው?
  • ለምን?
  • ታዲያ እንዴት መጣ?
  • ተጋብዞ ነዋ!
  • ተጋብዞ?
  • ለምን አይጋበዝም?
  • ከተጋበዘ አይቀርማ በደንብ መጋበዝ አለበት።
  • ምን?
  • ፍትፍት!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን የሚተካ ረቂቅ ተዘጋጀ

ከቫት ነፃ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ገደብ ተቀመጠለት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሃያ...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...

[ክቡር ሚኒስትሩ አየር መንገዱ ወጪ ቆጣቢ የሥራ እንቅስቃሴ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን በሚያሳድግበት ሁኔታ ላይ ከተቋሙ ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ትልቁ ወጪያችን ለነዳጅ ግዥ የሚውለው ነው። ክቡርነትዎ እንደሚገነዘቡት የዩክሬን ጦርነት የዓለም የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ አሻቅቧል። ቢሆንም አገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር ውስጥ...