- Advertisement -

የሕዝቡን ኑሮ ማቅለል እንጂ ማክበድ ተገቢ አይደለም!

መንግሥት አገር ሲያስተዳድር ለበርካታ ወጪዎቹ ገንዘብ ስለሚያስፈልጉት አስተማማኝ የገቢ ምንጮች ሊኖሩት ይገባል፡፡ በጀት ሲይዝም ሆነ ወጪዎቹን ሲያቅድ ጠንቃቃ መሆን ይኖርበታል፡፡ ወቅቱ ለመጪው ዓመት በጀት ረቂቅ ማቅረቢያ ስለሆነ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ መነጋገር ይገባል፡፡ መንግሥት ያለፈው ዓመት በጀቱ እንዳልበቃው፣ በርካታ ፕሮጀክቶችን ለመሰረዝ መገደዱን፣ በአንዳንድ ክልሎች ለመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ መክፈል እንዳቃተውና የመሳሰሉ የችግር ወሬዎች በስፋት ተሰምተዋል፡፡ መንግሥት የገንዘብ ችግር አጋጥሞታል ሲባል ጠቃሚ ምክረ ሐሳቦችን ማቅረብ ተገቢ ነው፡፡ መንግሥት በተቻለ መጠን አላስፈላጊ ወጪዎችን መቀነስ አለበት፡፡ ከወረዳ እስከ ፌዴራል መንግሥት ድረስ የሚከናወኑ የቅንጦት ግዥዎችና አንገብጋቢ ያልሆኑ ፕሮጀክቶች መቆም አለባቸው፡፡ በጥናት ላይ የተመሠረቱ አዋጭ የገቢ ምንጮችን ማስፋት ይጠበቅበታል፡፡ በከባድ የኑሮ ውድነት እየተደቆሰ ያለውን ሕዝብ ካለችው ከእጅ ወደ አፍ ገቢ ላይ፣ በተለያዩ መንገዶች ጫና በመፍጠር የተለያዩ የግብር ዓይነቶችን መቆለል ተገቢ አይደለም፡፡ መንግሥት የሕዝቡን ኑሮ ማክበድ አቁሞ ጤናማና ውጤታማ የገቢ ምንጮች ላይ ያተኩር፡፡

እየተለወጠ ካለው የዓለም ሥርዓት ጋር አብሮ መራመድ የግድ ነው፣ መሆንም አለበት፡፡ ከተለያዩ አገሮችም ሆነ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በሚኖር የሁለትዮሽም ሆነ የባለብዙ ግንኙነት፣ የራስን የቤት ሥራ በሚገባ አጠናቆ መነጋገርም ሆነ መደራደር ከመንግሥት ከሚጠበቁ ሥራዎች መካከል ይጠቀሳል፡፡ ለዚህ ደግሞ በተለያዩ መስኮች በተመሰከረላቸው ብቁ ባለሙያዎች መታገዝ አስፈላጊ ነው፡፡ ፖሊሲዎችም ሆኑ ስትራቴጂዎች ወቅቱን የዋጁ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ የጥቂቶችን ፍላጎት ከማስፈጸም በላይ አገራዊ ጥቅም ሊከበር የሚችለው፣ ከማናቸውም ተደራዳሪ አካላት ጋር በብቃት ጥቅምን ለማስከበር የሚያስችል ክህሎት ሲኖር ነው፡፡ መንግሥት የበጀት ጉድለትን ለመሸፈን፣ አማራጭ የገቢ ምንጮችን ለመቃኘት፣ ሕዝብ ላይ ጫና የሚያሳድሩ ዕርምጃዎችን እንዳወይስድና በሌሎች ኃይሎች እጁ እንዳይጠመዘዝ በጥናት ላይ የተመሠረቱ ሥራዎች ያስፈልጉታል፡፡ በጥናት ላይ ያልተመሠረቱ የዘፈቀደ ዕርምጃዎች ግን የሕዝቡን ኑሮ ከማክበድና ከማመሰቃቀል የዘለለ ፋይዳ እንደሌላቸው በስፋት እየታየ ነው፡፡ የተፈጥሮ ሀብቶችን ከፍተኛ መጠን ካለው የሰው ሀብት ጋር አቆራኝቶ ኢትዮጵያን የአፍሪካ ቅርጫ ማድረግ እየተቻለ፣ እያደር የድህነቱን አዘቅት ማስፋት የታሪክ ተጠያቂ ያደርጋል፡፡

መንግሥት ሙሉ ትኩረቱ መሆን ያለበት የቅንጦት ቤተ መንግሥቶችና መናፈሻዎች ላይ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የገቢ ምንጭና ሥራ ፈጣሪ ሊሆኑ የሚችሉ የተለያዩ መሠረተ ልማቶች ላይ ነው፡፡ ፕሮጀክቶች ሲታቀዱም የምግብ ችግርን የሚፈቱ፣ ንፁህ ውኃና የኤሌክትሪክ ኃይል በስፋት የሚያስገኙ፣ የሕዝብና የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎቶችን በብዛት የሚያቀርቡ፣ ለኢንዱስትሪ ጥሬ ዕቃዎችን በብዛትና በጥራት የሚያመርቱ፣ የግብርና ዘርፉን በአጭር ጊዜ የሚያዘምኑና የሚያስፈነጥሩ፣ ዘመኑ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ አቅም የሚያስታጥቁና የመሳሰሉ ሀብት ፈጣሪነት ላይ ማተኮር ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ በተረፈም መንግሥት በከፍተኛ ዲሲፕሊን ከአባካኝነት ወጥቶ ወጪ ቆጣቢ መሆን አለበት፡፡ በደሃ አቅም ደረጃ ሊታሰቡ የማይችሉ ዘመናዊ የቅንጦት ተሽከርካሪዎችና ሌሎች ውድ ቁሳቁሶችን ግዥ በፍጥነት ማስቆም የግድ ነው፡፡ የቅንጦት ግንባታዎችን እያካሄዱና በቅንጦት ኑሮ ውስጥ እየተቀማጠሉ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ለወደሙ መሠረተ ልማቶች መልሶ ግንባታና ተፈናቃዮችን ለማቋቋም የውጭ ዕርዳታ መጠየቅ እርስ በርሱ ይጣረሳል፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ሕዝብ በከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እየተመታ ቅንጦት ማሰብም ኢሞራላዊ ነው፡፡

በተደጋጋሚ ለማስታወስ እንደምንሞክረው ከዚህ በፊት የነበሩና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተፈጠሩ ችግሮችን ለማስወገድ ቅደም ተከተል ያስፈልጋል፡፡ በረጅም፣ በመካከለኛና በአጭር ጊዜ ሊፈቱ የሚችሉ ችግሮችን መለየት ይገባል፡፡ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ትኩረት ከሚፈልጉ ጉዳዮች መካከል ሰላም፣ የምግብ ዋስትና፣ መጠለያ፣ የሥራ ፈጠራና የመሠረተ ልማት አገልግሎቶች ከብዙ በጥቂቱ ናቸው፡፡ መንግሥት ሌሎች ጊዜ የሚሰጡ ፕሮጀክቶቹን ገታ አድርጎ መሠረታዊና አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ቢያተኩር ከመካከለኛ ኑሮ ወደ ድህነት፣ ከድህነት ወደ ባሰው ፍፁም ድህነት ውስጥ እየተንደረደሩ እየገቡ ያሉ ወገኖችን መታደግ ይችላል፡፡ ለዚህ ዕውን መሆን ደግሞ በተለይ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች በርካታ ወጣት የሰው ኃይል ሊያሰማራ የሚያስችል አዋጭ ፖሊሲ መንደፍ ነው፡፡ በተለመደው መንገድ መንደፋደፍ ከኪሳራ በስተቀር ምንም ዓይነት ትርፍ እንደማያስገኝ በሚገባ ታይቷል፡፡ የሕዝቡ ኑሮ ከዕለት ወደ ዕለት እየከበደ ሲሄድ፣ አዳዲስ አማራጮችን በባለሙያዎች ታግዞ ማየት ይገባል፡፡ 

- Advertisement -

በጀትን በአግባቡ አቅዶ ከአቅም ጋር የተገናዘቡ ሥራዎችን ማከናወን ከመንግሥት የሚጠበቅ ኃላፊነት ነው፡፡ በጀቱም ለአገር ልማትና ለሕዝብ የኑሮ ዕድገት ፋይዳ ሊኖረው ይገባል፡፡ መንግሥት ከመጠን በላይ እየተበደረ ገበያውን ሲያጨናንቀው ለዋጋ ግሽበት የራሱን አሉታዊ አስተዋፅኦ ያበረክታል፡፡ መንግሥት የግብር ሥርዓቱ ውስጥ ያልገቡ በርካቶችን ወደ መረቡ ጎትቶ ማምጣት ይጠበቅበታል፡፡ ከግብር ሰብሳቢዎች ጋር በመመሳጠር የሚሰውሩና የሚያጭበረብሩትን መንጥሮ ለሕግ ማቅረብ አለበት፡፡ በሐሰተኛ ደረሰኝ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ሀብት በሕገወጥ መንገድ የሚያግበሰብሱትን በብርቱ ክትትል በቁጥጥር ሥር ማዋል ይኖርበታል፡፡ አገሪቱን በኮንትሮባንድ የሚያስወርሩ እነ ማን እንደሆኑ ስለሚታወቅ ዕርምጃው ጠንካራ ሊሆን ይገባል፡፡ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ ሆነው አገርን ለዘራፊዎች የሚያጋልጡ ስግብግብ ሹማምንትን በሕግ አደብ ማስገዛት አለበት፡፡ በተጨማሪም ከአገልግሎት ፈላጊው ሕዝብ ላይ ጉቦ ከሚቀበሉ ነቀዞች ጀምሮ፣ የመንግሥት ሀብት ዘረፋ ላይ ተሰማሩትን በሙሉ ያለ ምንም ምሕረት ማጋለጥ ግዴታው ነው፡፡ ሕዝብ እንደ ሰደድ እሳት የሚግለበለበውን የኑሮ ውድነት መቋቋም ተስኖት፣ ጥቂቶች እንዳሻቸው የሚፈነጩበት ምንም ምክንያት የለም፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ከዕለት ወደ ዕለት ኑሮን እያከበዱ ካሉ ዋነኛ ጉዳዮች መካከል አንደኛው የምግብ ዋጋ ንረት ነው፡፡ የምግብ ዋጋ ከዓመት ወደ ዓመት በጣም እየጨመረ ከመሆኑም በላይ፣ በርካቶች ቤተሰቦቻቸውን በቀን ሦስቴ ቀርቶ አንዴም ለመመገብ ፅኑ ችግር ውስጥ ናቸው፡፡ የዋጋ ግሽበቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ ምክንያት ብዙዎች ሊቋቋሙት የማይችሉት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ናቸው፡፡ ከምግብ በተጨማሪ የቤት ኪራይና የሕክምና ወጪዎች የማይቀመሱ እየሆኑ ነው፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢኮኖሚው በደረሰበት ጉዳት ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ ተዳክሟል፡፡ የነዳጅና ከውጭ የሚገቡ መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎች ዋጋ ከሁለትና ከሦስት እጥፍ በላይ ውድ ሆኗል፡፡ ብሔራዊ ዓመታዊ ጠቅላላ ምርት በመቀነሱና የሥራ አጥነት ቁጥሩ እየጨመረ በመሆኑ፣ ለብዙዎች ሥራም ሆነ ገቢ ለማግኘት አዳጋች እየሆነባቸው ነው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እየከፋ በሄደ ቁጥር ዜጎች መሠረታዊ የፍጆታ ዕቃዎችንና አገልግሎቶችን ማግኘት ስለሚያዳግታቸው፣ ለከፋ ድህነት ከመጋለጣቸውም በላይ ማኅበራዊ ቀውስ እንዲቀሰቀስ ምክንያት ይሆናል፡፡ መንግሥት ሆይ የሕዝቡን ኑሮ ማቅለል እንጂ ማክበድ የበለጠ ችግር ፈጣሪ መሆኑን ተገንዘብ!

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የፖለቲካ ምኅዳሩ መላሸቅ ለአገር ህልውና ጠንቅ እየሆነ ነው!

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምኅዳር ከዕለት ወደ ዕለት የቁልቁለት ጉዞውን አባብሶ እየቀጠለ ነው፡፡ በፖለቲካ ፓርቲዎች የእርስ በርስ ግንኙነትም ሆነ በውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ የሚታየው መስተጋብር፣ ውል አልባና...

የመኸር እርሻ ተዛብቶ ቀውስ እንዳይከሰት ጥንቃቄ ይደረግ!

ክረምቱ እየተቃረበ ነው፡፡ የክረምት መግቢያ ደግሞ ዋናው የመኸር እርሻ የሚጀመርበት ጊዜ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከእርሻው ክፍለ ኢኮኖሚ 70 በመቶ ያህሉን የሰብል ምርት የምታገኘው በመኸር እርሻ...

ጠንካራና አስተማማኝ ተቋማት በሌሉበት ውጤት መጠበቅ አይቻልም!

በኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ የሚስተዋሉ መዛነፎችና አለመግባባቶች ዋነኛ ምክንያታቸው፣ ከበፊት ጀምሮ እስካሁን ድረስ ጠንካራና አስተማማኝ ተቋማትን ለመገንባት አለመቻል ነው፡፡ በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ፣ በፀጥታ፣...

ሰላም የሚሰፍነው ቅራኔን በማስወገድ እንጂ በማባባስ አይደለም!

ሕዝብና መንግሥት ለአገር ሰላም፣ ልማትና ዕድገት በጋራ ሲሠሩ ቅያሜም ሆነ ቅራኔ የሚፈጠርበት ዕድል የጠበበ ይሆናል፡፡ ሕዝብና መንግሥት ግን ሆድና ጀርባ ሲሆኑ ቅያሜ እየጨመረ ወደ...

መንግሥት ከድጋፍ በተጨማሪ ተቃውሞንም ማስተናገድ ይልመድ!

አገር የመምራት ዕድል ያገኘ መንግሥት ዋነኛ ተልዕኮው የሕዝብን ሰላምና ደኅንነት ማስጠበቅ፣ የአገርን ብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅሞች ማስከበር፣ ሕግና ሥርዓት ማስፈን፣ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ማክበር፣ በዜጎች...

በየዘርፉ የሚስተዋለው ሕገወጥነት በፍጥነት ይገታ!

ዜጎች አገልግሎት በሚያገኙባቸው መንግሥታዊ ተቋማትም ሆነ በሌሎች ሥፍራዎች፣ ከአቅማቸው በላይ ጉቦ ወይም መማለጃ እየተጠየቁ መሠረታዊ መብቶቻቸውን እየተነፈጉ ነው፡፡ የነዋሪነት መታወቂያ፣ የግንባታ ፈቃድ፣ የመሬትና ተያያዥ...

አዳዲስ ጽሁፎች

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ ግንቦት 21 ቀን 2015 ዓም በስካይ ላይት ሆቴል በተከበረው በዚሁ በዓል ላይ በርካታ አምባሳደሮችና ሌሎች...

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ መሆኑ ተደጋግሞ ይወሳል፡፡ ሃይማኖቶች ማኅበረሰቡን በሞራል ከማነፅ ጀምሮ ለአገር ግንባታ ያበረከቱት አስተዋጽኦ የማይተካ ነውም ይባላል፡፡...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ ፋብሪካ አክሲዮን ማኅበር በ2022 በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡ የኩባንያውን ዓመታዊ ክዋኔ...

የባንኮች ብድር አሰጣጥ ፍትሐዊና ብዙኃኑን ያማከለ እንዲሆን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አሳሰበ

ባንኮች የብድር አገልግሎታቸውን በተቻለ መጠን ፍትሐዊ፣ የብዙኃኑን ተጠቃሚነት ያማከለና በተለይም የአምራች ዘርፉን እንዲደግፍ ለማድረግ በትኩረት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምሕረቱ...

የነፃነት ዋጋ እንዴት ይተመናል?

የዛሬው ጉዞ ከሳሪስ አቦ ወደ ቃሊቲ መናኽሪያ ነው። የሰው ልጅ ለኑሮ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ጎዳናውን ሕይወት ዘርቶበታል። እንደ ወትሮው የኑሮ ንረት እያፍገመገመን እዚህ ደርሰናል። ‘ኑሮ...

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን