- Advertisement -

ፕላስቲክ የሚሰበስቡ የንግድ ልውውጥ የሚያደርጉበት የመረጃ መረብ

በየቦታው የሚጣሉ የፕላስቲክ ጠርሙሶች፣ ጀሪካን፣ ብረታ ብረት፣ ካርቶንና ሌሎች መሰል ግብዓቶች የመዲናይቷን ውበት አጥፍተውት ከርመዋል፡፡ በተለይም በመሀል ከተማ የሚገኙ ቦታዎች የችግሩ መገለጫ ሆነው ነበር፡፡ ችግሩን ለመቅረፍም በከተማዋ በውበትና ፅዳት ዘርፍ የሚሠሩ መንግሥታዊ ተቋማት እንዲሁም መንግሥታዊ ያልሆኑት ሲሠሩ ከርመዋል፡፡

በርካታ ማኅበራትም ከየጎዳናው የወዳደቁ ፕላስቲክ ነክና ብረታ ብረት በመሰብሰብና እነዚህን ግብዓቶች መልሶ በመጠቀም ዘርፍ እንዲሰማሩ ተደርጓል፡፡ ሆኖም የገበያ ትስስር ክፍተት አለ፡፡፡

ፔትኮ ኢትዮጵያ ከጂ አይ ዜድ ጋር በመቀናጀት በዚህ ሥራ ላይ የተሰማሩ መሪ ተዋናዮች እርስ በርስ የሚተዋወቁበት እንዲሁም የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት የመረጃ መረብ ሰኞ ግንቦት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል፡፡

የፔትኮ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ምሕረት ተክለ ማርያም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ አካባቢን የሚበክሉ የውኃ ፕላስቲኮችንና ሌሎች ግብዓቶችን ሰብስበው መልሶ ጥቅም ላይ የሚያውሉ የዘርፉ ተዋናዮች እርስ በርስ የሚገናገኙበት እንዲሁም የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበትን አማራጭ እንዲያገኙ የመረጃ መረብ ተዘርግቷል፡፡

በመረጃ መረብ ተጠቃሚ የሚሆኑት አዲስ አበባን ጨምሮ ከ18 የክልል ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ መቶ ድርጅቶች መሆናቸውን የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጇ፣ ድርጅቶቹ የድርጅታቸውን ሙሉ መረጃ በትክክለኛ መንገድ በማስመዝገብ የዲጂታሉ ፕላትፎርም ወይም የኢንዱስትሪው አካል መሆን እንደሚችሉ አስረድተዋል፡፡

በዚህ መሠረት በዘርፉ የተሰማሩ ተቋሞች የመረጃ መረቡን በመጠቀም ትክክለኛ መረጃን እንዲያገኙ፣ የገበያ ትስስርን እንዲፈጥሩና በኢንዱስትሪው ዙሪያ የሚሠሩ ሥራዎችን ወቅታዊ መረጃ እንዲያገኙ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ሲሉ አክለዋል፡፡

- Advertisement -

በኢንዱስትሪው የተሰማሩ ተዋናዮች የተለያዩ ችግሮች እንደሚገጥማቸው ያስታወሱት ወ/ሮ ምሕረት፣ ችግሮችን ለማለፍ የተዘረጋው የመረጃ መረብ የሚያግዛቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የመረጃ መረቡም በፕላስቲክ ኢንዱስትሪው ውስጥ ያሉ ተዋናዮች ወይም ባለድርሻ አካላት ከፕላስቲክ አምራቾች ጀምሮ እስከ መጨረሻው መልሶ መጠቀም ድረስ የተሰማሩ አካላት እርስ በርስ የሚገናኙበት መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የተዘረጋውን የመረጃ መረብ በታለመለት ዓላማ መሠረት ከግብ ለማድረስ አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ሁኔታዎች እንዳሉትና እነዚህን ተግባራዊ ለማድረግ ተቋሙ ከዘርፉ ተዋናዮች ጋር የሚሠራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

እስካሁን ለአገር ውስጥና ለውጭ የሚያቀርቡ መቶ ድርጅቶች መመዝገባቸውን፣ በቀጣይም ይህንን አሠራር በማጠናከር በርካታ ተቋሞችን ለመመዝገብ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን አስረድተዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ተዋናዮች የሚገጥማቸው ችግር የቦታ ይዞታና የትራንስፖርት አገልግሎት መሆኑን የተናገሩት ዋና ሥራ አስኪያጇ፣ መፍትሔዎችን ለማመቻቸት ተቋሙ ከተለያዩ መንግሥታዊ ተቋሞች ጋር ውይይት እያደረገ ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የፕላስቲክ ተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን፣ የተለያዩ ጥናቶችም እ.ኤ.አ. ከ2006 እስከ 2021 ባለው ጊዜ የፕላስቲክ ተጠቃሚዎች ቁጥር በ13 በመቶ መጨመሩን እንደሚያሳዩ ገልጸዋል፡፡

ፕላስቲክን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ የአገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አንድ ዕርምጃ ከፍ ማድረግ እንደሚቻል፣ ይሁን እንጂ ይህንን ተፈጻሚ ማድረግ ካልተቻለ ለአካባቢያዊ፣ ማኅበራዊና ሌሎች ችግሮች ተጋላጭ እንደሚኮን ወ/ሮ ምሕረት ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ የፕላስቲክ ቆሻሻን መልሶ ከመጠቀም አኳያ ይኼ ነው የሚባል ሥራ አለመሠራቱን ጠቅሰው፣ አሁን ላይም በዚህ ሥራ ላይ የተሰማሩ ተቋሞች አዲስ አበባና በአዲስ አበባ ዙሪያ ፋብሪካቸውን ተክለው የሚሠሩ ናቸው ሲሉ አብራርተዋል፡፡

በአገሪቱ የፕላስቲክ ብክለት ሲታይ ከአዲስ አበባ ውጭ ጭምር እንዳለና ይኼም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በመልሶ መጠቀም የተሰማሩ ድርጀቶችም፣ ተቋማቸውን በማስፋት ከአዲስ አበባ ውጭ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ፋብሪካቸውን በመትከል መሥራት እንደሚገባና ይህንን የቤት ሥራ ለመወጣት ተቋሙ የሚሠራ መሆኑን  ገልጸዋል፡፡

በፕላስቲክ ኢንዱስትሪው የሕግና የፖሊሲ ሥርዓቶችን በተሻለ ሁኔታ በመዘርጋት መሥራት እንደሚገባና እነዚህን ጉዳዮች ተፈጻሚ ለማድረግ መረጃዎች የማሰባሰብ ሥራ እየተሠራ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍሬነሽ መኩሪያ እንደገለጹት፣ የተለያዩ የፕላስቲክ ውጤቶችን መልሶ በመጠቀም የአገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ከፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

የፕላስቲክ ምርቶችን በዘላቂነት መያዝ ካልተቻለ በማኅበረሰቡ ዘንድ የሚያደርሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን፣ ይሁን እንጂ ፕላስቲክን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ትልቅ ሀብት ነው ብለዋል፡፡

ፕላስቲክን መልሶ በመጠቀም ዙሪያ የሚሠሩ ሥራዎች ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ የካርቦን ልቀትንና የአካባቢ ብክለትን መቀነስ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ በመልሶ መጠቀም ላይ የተሰማሩ ተቋሞች በበርካታ ችግሮች ውስጥ ያሉና እንደ ሌሎች አገሮች በዘርፉ ውጤታማ ሥራ እየተመዘገበ አለመሆኑን አክለዋል፡፡

ፕላስቲክ፣ ብረታ ብረትና ሌሎች ግብዓቶችን መልሶ በመጠቀም ላይ የተሰማሩ የዘርፉ ተዋናዮች የተሻለ አገልግሎት እንዲያገኙ እንዲሁም እርስ በርስ የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ አሁን የተዘጋጀው ፕላት ፎርም ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የሪፍት ቫሊ ቴክኖሎጂ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር መሥራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አደን ዳርጌ ተናግረዋል፡፡

ፕላት ፎርሙም የተለያዩ አገልግሎቶችን እንዲያገኙበት ምቹ ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ባለፈ በአሁኑ ወቅት ለመልሶ መጠቀም የሚውሉ ግብዓቶች በአገሪቱ ውስጥ በምን ያህል ገንዘብ እየተሸጠ ነው? የሚለውን ለማወቅ ጭምር እንደሚረዳቸው ዋና ሥራ አስኪያጁ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

በተለይም በአገር አቀፍ ደረጃ የሚገኙ ሻጭና ገዥ እርስ በርስ የሚተዋወቁበት ፕላት ፎርም መሆኑን የተናገሩት መሥራቹ፣ የትኛው ክልል ላይ ምን ያህል ግብዓት አለ? የሚለውን ለመለየት በቀላሉ ይረዳል ብለዋል፡፡

በፕላት ፎርሙ ውስጥም የሚመዘገቡ የዘርፉ ተዋናዮች ሕጋዊነታቸው ሳይታወቅ ወደ ሥርዓት ውስጥ እንደማይገቡ ገልጸው፣ ይህንን ፕሮጀክት ወጥ በሆነ መንገድ ለማስቀጠል ከፔትኮ ኢትዮጵያ ጋር በጋራ ለመሥራት ለአራት ዓመታት የሚቆይ ስምምነት ማድረጋቸውን አብራርተዋል፡፡

የሶዶ ደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ኅብረት ሥራ ማኅበር አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ዶክተር  እንደገለጹት፣ ከዚህ በፊት በርካታ ፕላስቲኮች ተሰብስበው ለማን እንደሚሸጥ ግራ ይገባ ነበር፡፡ ጀሪካን፣ የፕላስቲክ ጠርሙስ፣ ብረታ ብረትና ሌሎች ግብዓቶችን ሰብስበው ሐዋሳ ለሚገኙ ድርጅቶች በእርካሽ ዋጋ ይሸጡም ነበር፡፡

በአሁኑ ወቅት በፔትኮ ኢትዮጵያ በኩል የተፈጠረው ፕላት ፎርም የሰበሰቡትን ግብዓት ለማንና እንዴት መሸጥ እንዳለባቸው የሚያሳይ በመሆኑ፣ ሥራቸውን እንደሚያቀል ገልጸዋል፡፡

በመንግሥት በኩል ምንም ዓይነት ድጋፍ እንደማይደረግላቸው የገለጹት አስተዳዳሪው፣ አብዛኛው ደንበኞችም የግንዛቤ እጥረት ስለነበረ ደረቅ ቆሻሻ የመለየት ሥራ ላይ ሲቸገሩ ነበር ብለዋል፡፡

ማኅበሩ ብረትና ጀሪካን በኪሎ እስከ 50 ብር በመሸጥ ላይ መሆኑን፣ እስካሁንም የተለያዩ ግብዓቶችን በመሸጥ ውጤታማ ሥራ መሥራቱን ገልጸዋል፡፡

በዘርፉ የተሰማሩ ተዋናዮች የግብዓት፣ የቦታ ይዞታና የተለያዩ ችግሮች እንደሚገጥሟቸው፣ የእነሱ ማኅበርም የዚህ ችግር ገፈት ቀማሽ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አዲስ አበባ ፅዱ እንድትሆን ማኅበረሰቡ የደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓትን በሚገባ እንዲያውቅ የተዘረጋው የመረጃ ቋት ትልቅ ጠቀሜታ አለው ያሉት የጥበብ ፅዱና አረንጓዴ ደረቅ ቆሻሻ አሰባሰብና አወጋገድ መልሶ መጠቀም ኅብረት ሽርክና ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍቅሬ ገብሬ ናቸው፡፡

ፔትኮ ኢትዮጵያና ጂ አይ ዜድ በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ፕላት ፎርም ከጥሬ ሀብት ጀምሮ እንዴት መልሶ መጠቀም አለብን? የሚለውን ለማወቅ የሚረዳ መሆኑን አቶ ፍቅሬ ገልጸዋል፡፡

በቀጣይ በዚህ ሥራ የተሰማሩ የዘርፉ ተዋናዮች እንዴት ተቀናጅተው መሥራት እንዳለባቸው ለማወቅ የተዘረጋው ፕላት ፎርም ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው፣ ማኅበሩም እስካሁን የተለያዩ ግብዓቶች በመሰብሰብ በመልሶ መጠቀም ለተሰማሩ ድርጅቶች እያስረከበ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በየጊዜው በርካታ ግብዓቶችን በጥሬው በመሰብሰብ ኮባ ኢምፓክት ለተሰኘ ድርጅት እያቀረቡ መሆኑን፣ ወደፊት ግን የፕላስቲክ ጠርሙሱን ጨፍልቆ ለማስረከብ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን አስታውሰዋል፡፡

በቀጣይ መንግሥት የራሳቸው የመልሶ መጠቀም ፋብሪካ እንዲገነቡ የቦታ ይዞታ እንዲሰጣቸው መጠየቃቸውን፣ እስካሁን በሳምንት ሃያ ሺሕ ኪሎ በመሰብሰብ ኮባ ለተሰኘ ድርጅት እንደሚያቀርቡ አክለው ገልጸዋል፡፡

አንዳንድ ጊዜ የግብዓት እጥረት እንደሚያጋጥማቸውና እጥረቱም ሲያጋጥማቸው በ15 ቀን አንድ ጊዜ የሚያቀርቡበት ሁኔታ እንዳለ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በአገር አቀፍ ደረጃ በርካታ ተቋሞች በዚህ ሥራ ቢሰማሩም እርስ በርስ ከመተዋወቅ አንፃር ችግር እንዳለ፣ ይኼንን ለመፍታት አሁን የተዘረጋው ፕላትፎርም የተሻለ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የባሕር ዳርና ድሬዳዋ ኤርፖርቶች የሲቪል በረራዎች ቁጥጥር ስርዓታቸውን አሳደጉ

በኢትዮጵያ ከሚገኙት አራት ዓለም አቀፍ ኤርፖርቶች መካከል የሆኑት የባህር ዳርና የድሬዳዋ ኤርፖርቶች፣ የአየር በረራዎች ቁጥጥር ክፍሎች ከጥር ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ማናቸውንም እስከ 25...

አዳዲስ የሕክምና ቴክኖሎጂዎች እንደሚተዋወቁበት የሚጠበቀው መድረክ

በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን የሕክምና አገልግሎት ፍላጎት ለማሳካት የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችና መፍትሔዎችን የሚያቀርቡ በአሥር አገሮች የሚገኙ ኩባንያዎች ይሳተፉበታል የተባለው ዘጠነኛው ኢትዮ ሄልዝ ዓውደ ርዕይ ከየካቲት...

የአየር ንብረት ለውጡን ጫና ለመቋቋም

በመስኖ ልማትና አየር ንብረት ለውጥ ላይ የተሻለ ትብብርና ግንኙነቶችን ለመፍጠር ያስችላል የተባለ ዓለም አቀፍ ‹‹የመስኖና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ምርታማነት ጉባዔ›› ከየካቲት 5 እስከ...

ለጤና ተቋማት አክሬዲቴሽን ለመስጠት ዝግጅት እየተጠናቀቀ መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አክሬዲቴሽን አገልግሎት ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለጤና ተቋማት አክሬዲቴሽን ለመስጠት ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን አስታወቀ፡፡ የሊያና ሔልዝ ኬር (ያኔት ሆስፒታሎች) አራት ዓለም አቀፍ የዕውቅና ምስክር...

ሴት ሥራ ፈጣሪዎች በብሩህ እናት 2017 ውድድር እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ

ሴት ሥራ ፈጣሪዎች  የፈጠራ ሥራቸውን ለማጎልበት፣ የቢዝነስ ክህሎታቸውን ለማሳደግና የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት በሚረዳቸው የብሩህ እናት 2017 የንግድ ሥራ ፈጠራ  ውድድር እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ፡፡ የሥራና ክህሎት...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን