Saturday, September 30, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ለባለቤታቸው ስለሰላም አስፈላጊነትና ስለመንግሥት አቋም እያስረዷቸው ነው] 

  • መንግሥት ስለሰላም አብዝቶ የሚናገረው ለምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?
  • ኧረ ጨርሶ ሲናገር ሰምቼ አላውቅምኧ ይናገራል እንዴ?
  • እንዴታ፡፡
  • ስለሰላም ይናገራል?
  • አዎ፣ የመንግሥትም ሆነ የፓርቲያችን የሙሉ ጊዜ ሥራ በሰላም ላይ ነው።
  • ይህንን አላውቅም ነበር።
  • ለምን ይመስልሻል በዚህ ልክ ስለሰላም ከፍተኛ ትኩረት የሰጠነው?
  • እንኳን ምክንያቱን ትኩረት መስጠታችሁንም አላውቅም እያልኩህ?
  • የሰላም ጉዳይ ዋናው ትኩረታችን ነው ስልሽ፣ ቆይ ለምን እንደሆነ ላስረዳሽ።
  • እህ…
  • ሰላም የሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ ነው።
  • እህ… ለዚያ ነው?
  • አዎ፣ ምክንያቱም ሰላም ከሌለ ተቃራኒው ነው የሚኖረው።
  • ተቃራኒው ምንድነው?
  • ግጭትና ጦርነት ነዋ።
  • አዎ፣ ልክ ብለሃል።
  • ግጭትና ጦርነት ደግሞ የዜጎችን ደኅንትና ነፃነት አደጋ ላይ ይጥላሉ።
  • እህ… ለሰላም ትኩረት የሰጣችሁት በዚህ ምክንያት ነው?
  • በዚህ ብቻ አይደለም፣ ሌሎችም ምክንያቶች አሉ።
  • ምንድናቸው?
  • ቅድም ግጭትና ጦርነት የዜጎችን ደኅንነትና ነፃነት አደጋ ላይ ይጥላሉ ነበር ያልኩሽ አይደል?
  • አዎ።
  • ሌላው ደግሞ ግጭትና ጦርነት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ያውካሉ።
  • አሃ… በዚህ መልኩ አልተረዳሁትም ነበር።
  • ይኼ ብቻ መስሎሽ ነው?
  • እ…?
  • ግጭትና ጦርነት ካለ የሰው ልጆች ሕይወት ይቀጥፋል፣ ሀብትና ንብረትም ይወድማል።
  • እህ… ለዚህ ነዋ መንግሥት ለሰላም ትኩረት የሰጠው?
  • በሚገባ፣ አለበለዚያማ ይቻልም።
  • ምንድነው የማይቻለው?
  • ብልፅግናን ማረጋገጥ።
  • አሃ… እንደዚያ ነው?
  • አዎ፣ አዲሱ የፓርቲያችን ፍልስፍናም በዚህ ላይ ተመሥርቶ የተቀረፀ ነው።
  • አዲሱ ፍልስፍና ምንድነው የሚለው?
  • ግጭትና ጦርነት የብልፅግና ፀር ናቸው የሚል ነው።
  • እጅግ ጥሩ የአስተሳሰብ ለውጥ ነው ያደረጋችሁት።
  • የአስተሳሰብ ለውጥ አድርገን አይደለም።
  • እህ…?
  • የፓርቲያችን ተፈጥሯዊ ባህሪይ ነው።
  • እንደዚያ ነው?
  • እየነገርኩሽ፣ ትጠራጠሪያለሽ እንዴ?
  • መጠራጠሬ ሳይሆን ትዝ ብሎኝ ነው።
  • ምኑ?
  • ያሳለፍናቸው ሦስት ዓመታትና…
  • እና ምን?… ቀጥይ
  • አሁን ያለንበት ሁኔታ አንተ ከምትለው ጋር አልታረቅ ብሎኝ ነው።
  • ለምን አልታረቅ ይልሻል? ምን ለማለት ፈልገሽ ነው?
  • ሰላም የሙሉ ጊዜ ሥራችን ነው ብትሉም፣ አሁንም በተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶች አሉ ብዬ ነው።
  • ግጭቶች ቢኖሩስ?
  • ግጭትና ጦርነት የብልፅግና ፀር ነው ብለኸኝ አልነበርም እንዴ ቅድም?
  • አዎ።
  • ጠመንጃ ይዘው በየአካባቢው የሚታገሉ ባሉቡት ሁኔታ የምትሉት ሰላም እንዴት ሊመጣ እንደሚችል እያሰብኩ ነው።
  • ይመጣል፣ ቀላል ነው።
  • ቀላል ነው?
  • አዎ፣ በጣም ቀላል ነው።
  • እንዴት?
  • የአገር ሽማግሌዎችንና የሃይማኖት አባቶችን በመጠቀም ወደ ሰላም እንዲመጡ ጥሪ እናቀርባለን።
  • ጥሪውን ካልተቀበሉስ?
  • እንደመስሳቸዋለን!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...

ማን በማን ላይ ተስፋ ይኑረው?

በአንድነት ኃይሉ ችግሮቻችንን ለይተን ካወቅን መፍትሔውንና ተስፋ የምናደርግበትን ማወቅ እንችላለን፡፡...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ሳምንት ያክል የፓርቲ ስብሰባ ላይ ቆይተው አመሻሹ ላይ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ባለቤታቸው በአግራሞት ተቀብለው ስለቆይታቸው ይጠይቋቸው ጀመር]

እኔ እምልክ...? ውይ... ውይ... በመጀመሪያ እንኳን በሰላም መጣህ፡፡ እሺ ...ምን ልትጠይቂኝ ነበር? ይህን ያህል ጊዜ የቆያችሁት ለስብሰባ ነው? ስብሰባ ብቻ አይደለም። ከስብሰባ ውጪ ምን ነበር? በተለያዩ መሪ ሐሳቦች የተዘጋጁ ሥልጠናዎችን...

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን የፓርቲያቸውን የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ሲመለሱ ቢሯቸው ውስጥ አማካሪያቸው አንድ ጽሑፍ በተመስጦ እያነበበ አገኙት]

ምንድነው እንደዚህ መስጦ የያዘህ ጉዳይ? መጡ እንዴ ክቡር ሚኒስትር፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያወጣውን መግለጫ እያነበብኩ ነው፡፡ ግን እኮ ፊትህ ላይ የመገረም ስሜት ይነበባል፡፡ አዎ፣ መግለጫው ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ እየጠራ ያለውን ሞባይል ስልካቸውን ተመለከቱ፣ የህዳሴ ግድቡ ተደራዳሪ መሆናቸውን ሲያውቁ ስልኩን አነሱት]

ሃሎ... ጤና ይስልጥኝ ክቡር ሚኒስትር? ጤና ይስልጥልኝ ክቡር ተደራዳሪ... የጥረትዎን ፍሬ በማየትዎ እንኳን ደስ አለዎት፡፡ እንኳን አብሮ ደስ አለን፣ ምን ልታዘዝ ታዲያ? የውኃ ሙሌቱንና አጠቃላይ የግድቡን የግንባታ ሁኔታ...