Saturday, September 23, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ የፖለቲካ አማካሪያቸው እንዲፈጽም ባዘዙት አንድ ሚስጥራዊ ኃላፊነት ጉዳይ ላይ እየተወያዩ ነው]

  • ነገሩ በዕቅዳችን መሠረት ጥሩ ውጤት ያመጣ ይመስለኛል፣ ትክክል ነኝ?
  • በሚገባ ክቡር ሚኒስትር፣ ሴትየዋ ከሞላ ጎደል ያቀድናቸውን በሙሉ አድርገውታል።
  • መቼም አንተ ተዓምረኛ ሰው ነህ፣ ለመሆኑ እንዴት ስትል አሰብከው?
  • ሴትየዋን አውቃቸዋለሁ፣ ማንም ሰው በሕግ ጉዳይ እንዲመጣባቸው አይፈልጉም፣ ሲበዛ ወግ አጥባቂ ናቸው።
  • ማንም በሕግ ጉዳይ እንዲመጣባቸው አይፈልጉም ስትል ምን ማለትህ ነው?
  • ሕግን የሚፃረር ነገር ሊፈጽሙ ቀርቶ በሐሳብ ደረጃ እንኳን ለመወያየት አሻፈረኝ የሚሉ መሆናቸውን አውቃለሁ።
  • እሺ?
  • ስለዚህ የተሰረዘው ፓርቲ ሕጋዊ ሰውነት እንዲመለስ መንግሥት አዟል አልኳቸው።
  • እሺ?
  • እንደጠበቅኩት በቁጣ ቱግ አሉ።
  • እሺ?
  • ከዚያ የትኛው መንግሥት ነው ይህንን ያዘዘው ብለው ጠየቁኝ።
  • እሺ?
  • እኔም ያዘዙት ክቡር ሚኒስትሩ መሆናቸውን አሳወቅኳቸው።
  • እሺ?
  • እርሳቸው እኔን ሊያዙኝ አይችሉም የሚል በቁጣ የታጀበ ምላሽ ሰጡኝ።
  • በሌላ ቀን ደውዬ ተረጋግተን እንድንወያይ ጠየቅኳቸውና ቀጠሮ ያዝን፣ በቀጠሮው መሠረትም መንግሥት ለአገር ሰላም ሲባል ዓለም አቀፍ ግዴታ ጭምር የተገባበት ጉዳይ በመሆኑ እንጂ ጣልቃ ለመግባት ተፈልጎ እንዳልሆነ አስረዳኋቸው፡፡
  • እሺ?
  • ይህንን ካረጋገጥኩላቸው በኋላ በጣም ተረጋጉና እንደዚያ ከሆነ ሕግን በማይጥስ መንገድ መፈጸም እንደሚቻል ገለጹልኝ።
  • እንዴት? ምን ብለው?
  • አንድ አንቀጽ የሕግ ማሻሻያ በፍጥነት ተዘጋጅቶ በፓርላማ በማፅደቅ የፓርቲውን ሕጋዊ ህልውና መመለስ እንደሚቻል አስረዱኝ።
  • እኛስ ይኼን ማድረግ እንደሚቻል ጠፍቶን መስሏቸው ነው?
  • እንደዚያ መሆኑ ነው… ዕቅዳችን ፈጽሞ አልገባቸውም።
  • እሺ፣ ከዚያ በኋላስ?
  • ባቀረቡት ምክረ ሐሳብ ላይ ተነጋግሬ እንደማሳውቃቸው ገልጬላቸው ተሰናበትኩና ከቀናት በኋላ መልሰን ተገናኘን።
  • እሺ… ምን አደረግክ?
  • ያቀረቡት ሐሳብ ተቀባይነት እንዳላገኘና በታዘዙት መሠረት የፓርቲው ሕጋዊ ሰውነት እንዲመለስ መወሰኑን ነገርኳቸው።
  • እሺ?
  • በንዴት ጦፉ… መናገር አቃታቸው፣ በኋላ የተባለውን ፈጽሞ እንደማይቀበሉና እንደማያደርጉ ገለጹልኝ።
  • እሺ… ከዚያ ምን አደረግህ?
  • ውሳኔውን ተቀብለው የማይፈጽሙ ከሆነ አንድ አማራጭ ብቻ እንደሚኖራቸው፣ እሱም በፈቃዳቸው ከኃላፊነት መልቀቅ መሆኑን ገለጽኩላቸው።
  • ምን አሉ?
  • ያንን ማድረግ አትችሉም… መንግሥት አይደለም የሾመኝ… ተጠሪነቴም ለመንግሥት አይደለም አሉኝ።
  • እሺ ቀጥሎ ምን አደረግህ?
  • በፈቃድዎት መልቀቂያ የማያቀርቡ ከሆነ የቦርድ አመራሮች የሚነሱበትን ሕጋዊ ሥነ ሥርዓት ለመጠቀም እንገደዳለን አልኳቸው።
  • እንደዚያ ስትላቸው ምን አሉ?
  • ለተወሰነ ደቂቃ በዝምታ ተወጥው ከቆዩ በኋላ የፈለጋችሁትን ማድረግ ትችላላችሁ ብለው ጥለውኝ ወጡ።
  • እሺ… ከዚያ በኋላ ምን ተፈጠረ?
  • ከሁለት ቀናት በኋላ ደውለው ሊያገኙኝ እንደሚፈልጉ ገለጹልኝና ተገናኘን።
  • እሺ… ለምንድነው ለመገናኘት የፈለጉት?
  • እንደሚደውሉልኝ እርግጠኛ ነበርኩ፣ እንደጠበቅኩትም ሐሳባቸውን መቀየራቸውን ገለጹልኝ።
  • የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ?
  • ኧረ በጭራሽ፡፡
  • እ…?
  • መልቀቂያ ለማስገባት ነው።
  • ለካስ እንደዚህ ግትር ናቸው።
  • ክቡር ሚኒስትር… ሴትየዋ በዚህ ባህሪያቸው የሚታወቁ በመሆኑ እኮ ነው ይህንን አጋጣሚ እንድንጠቀምበት የጠየቅሁዎት።
  • አንተ መለኛ ነህ፣ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ማለት ይህ ነው፣ ግን አንድ ያልተመለሰ ነገር አለ።
  • ምን?
  • የቀሩት አመራሮችስ የሴትየዋን መርህ ተከትለው የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ለመመለስ ፈቃደኛ ባይሆኑስ?
  • እኛም በቀጥታ ሕጋዊ ሰውነቱን መልሱ አንላቸውም።
  • እና ምን ለማድረግ ነው ያቀድከው?
  • በአዋጁ ላይ አንድ ማሻሻያ አንቀጽ ማፀደቅ።
  • ምን የሚል ማሻሻያ አንቀጽ?
  • አንድ ፓርቲ ነፍጡን ጥሎ በሰላም ለመታገል ከመንግሥት ጋር ከተስማማ ሕጋዊ ሰውነቱ ይመለስለታል የሚል።
  • ይኼ ሴትየዋ ያቀረቡት ሐሳብ አይደለም አንዴ?
  • በፊት ነበር፣ አሁን ግን የሴትየዋ አይደለም፡፡
  • እንዴት?
  • ለቀዋል!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...

በሰጥቶ መቀበል መርህ መደራደርና ሰላም ማስፈን ለምን ያቅታል?

በያሲን ባህሩ አገር ግንባታ የትውልድን ትልቅና ታሪካዊ ኃላፊነት የሚጠይቅ ተግባር...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን የፓርቲያቸውን የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ሲመለሱ ቢሯቸው ውስጥ አማካሪያቸው አንድ ጽሑፍ በተመስጦ እያነበበ አገኙት]

ምንድነው እንደዚህ መስጦ የያዘህ ጉዳይ? መጡ እንዴ ክቡር ሚኒስትር፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያወጣውን መግለጫ እያነበብኩ ነው፡፡ ግን እኮ ፊትህ ላይ የመገረም ስሜት ይነበባል፡፡ አዎ፣ መግለጫው ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ እየጠራ ያለውን ሞባይል ስልካቸውን ተመለከቱ፣ የህዳሴ ግድቡ ተደራዳሪ መሆናቸውን ሲያውቁ ስልኩን አነሱት]

ሃሎ... ጤና ይስልጥኝ ክቡር ሚኒስትር? ጤና ይስልጥልኝ ክቡር ተደራዳሪ... የጥረትዎን ፍሬ በማየትዎ እንኳን ደስ አለዎት፡፡ እንኳን አብሮ ደስ አለን፣ ምን ልታዘዝ ታዲያ? የውኃ ሙሌቱንና አጠቃላይ የግድቡን የግንባታ ሁኔታ...

[የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሩ ክቡር ሚኒስትር ሌሊቱን በእንቅልፍ ልባቸው በህልም እየተወራጩ ሳለ የሞባይል ስልካቸው ጥሪ አነቃቸው። አለቃቸው ስለነበሩ ስልኩን በፍጥነት አነሱት]

በሌሊት ስለደወልኩኝ ይቅርታ፡፡ ችግር የለውም ክቡር ሚኒስትር፣ ምን ልታዘዝ? አንድ የአውሮፓ ባለሥልጣን ነገ በጠዋት ወደ አዲስ አበባ ይገባል። እሺ። ሌሎች የመንግሥት አመራሮች ስላልቻሉ እርስዎ መንግሥትን ወክለው ቦሌ ኤርፖርት...