ከስድስት አሠርታት በፊት ታላቁ ኢትዮጵያዊ ርዕሰ ኪነጠቢብ አፈወርቅ ተክሌ፣ በሞስኮ ከተማ የመጀመርያውን ዓውደ ርዕያቸውን አቅርበው ነበር፡፡ እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ፣ በያኔዋ ሶቪየት ኅብረት (የአሁኗ ሩሲያ) በ1956 ዓ.ም. በከፈቱት የሥዕል ዓውደ ርዕይ ከተገኙት ታላላቅ እንግዶች መካከል፣ የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የነገረ መለኮት (ቴዎሎጂ) ሊቅ ኮንስታንቲን ሩዝሂትስኪ እና በቦልሾይ ቴአትር የሶቪየት ባሌት ደናሿ ቲክሆሚርኖቫ ይገኙበታል፡፡ በፎቶዎቹ የኔታ አፈወርቅ ተክሌ ከሁለቱ ዕውቆች ጋር ሁነው ይታያሉ፡፡
- ፎቶ ከማኅበራዊ ትስስር ገጽ