Saturday, January 18, 2025

[በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለክትትልና ግምገማ የተሰማሩት ከፍተኛ አመራሮች ያገኙትን ውጤት ሪፖርት ያደረጉበት የቴሌቪዥን ፕሮግራምን የሚኒስትሩ ባለቤት ለብቻቸው በመገረም እየተከታተሉ ሳለ ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ዘለቁ] 

  • እኔ ብቻ ይሆን ግን እንዲህ የምሆነው?
  • ምን ሆንሽ?
  • ግርም፣ ብግን የሚያረገኝ?
  • ምንድነው ያስገረመሽ?
  • የምትሠሩት ነገር ሁሉ ግርም ይለኛል።
  • እንዴት… ምን ሰምተሽ ነው?
  • ውይይቱ ላይ የሚባሉት ነገሮች ናቸው?
  • ምን ሲባል ሰምተሽ ነው?
  • ክልሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የመደመር ትውልድ መጽሐፍ በመሸጥ 360 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ቢያቅድም እስካሁን የሰበሰበው ግን 25 ሚሊዮን ብር ብቻ ነው ይላሉ።
  • እና…?
  • እናማ በቀሪዎቹ ሐምሌና ነሐሴ ወራት መጽሐፉን ለማኅበረሰቡ በስፋት በመሸጥ ያቀዱትን ገቢ እንዲሰበስቡ ከክልሉ አመራሮች ጋር ተግባብተናል ይላሉ።
  • ታዲያ ይኼን ማለታቸው ምን ያስገርማል?
  • የክልሉ ማኅበረሰብ አርሶ አደር መሆኑን አስቤ ነዋ?
  • አርሶ አደር ቢሆንስ?
  • የእርሻ ወቅት ሳያልፍ ማዳበሪያ ይቅረብልኝ ብሎ ሰላማዊ ሠልፍ ለወጣ አርሶ አደር ምን ሊቀርብለት እንደሆነ አስቤ ነዋ?
  • ምን ሊቀርብለት ነው?
  • የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ነዋ!
  • እያሾፍሽ ነው?
  • ኧረ በጭራሽ! ኧረ ሌላም ጉድ አለ። ሚኒስትሩ የሚሉትን ስማ …
  • ሰማሃቸው?
  • በቅጡ አልሰማሁም፣ ምን አሉ?
  • ሆሆ… መቼም ዘንድሮ ጉድ ነው የምሰማው።
  • ምንድነው ያሉት?
  • የሐረሪ ክልል የጠቅላይ ሚኒስትሩን የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሸጦ በሚያገኘው ገቢ የሚተገብረውን ፕሮጀክት እየገለጹ ነበር።
  • እኮ ምን አሉ? ፕሮጀክቱ ምንድነው?
  • የመደመር ትውልድ መጽሐፍን ሸጦ በሚያገኘው ገቢ የጅብ ምገባ ትርዒትን ያለማል ነው የሚሉት።
  • ታዲያ ምኑ ነው ያስገረመሽ?
  • የምታቅዱት ፕሮጀክቶች ናቸዋ!
  • እንዴት? ይኼ ምን ያስገርማል?
  • ማኅበረሰቡ የሚቀምሰው ተቸግሮ እያማረረና የኑሮ ውድነት ትርዒት እየሠራበት መሆኑ ጠፍቶህ ነው?
  • የኑሮ ውድነት ችግር መኖሩንማ መንግሥትም አልካደም።
  • እሱ እኮ ነው የሚገርመኝ?
  • ምኑ?
  • መንግሥት የማኅበረሰቡን መሠረታዊ ችግር እያወቀ የጅብ ምገባ ትርዒት ለማበልፀግ ፕሮጀክት መንደፉ።
  • ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሥራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ጠፍቶሽ ነው?
  • እንዴት ሆኖ?
  • ለምን አይሆንም?
  • በጅብ ምገባ የሥራ ዕድል ለመፍጠር?
  • አዎ!
  • ቢፈጠር እንኳ የሥራ ዕድል ነው ለማለት ይቸግረኛል።
  • ለምን?
  • ጅብ የመመገብ የሥራ ዕድል መጨረሻው አያምርም።
  • ለምን?
  • መንግሥት በጀት አጠረኝ ብሎ ምግብ ማቅረቡን ያቋረጠ ቀን ምን ሊፈጠር እንደሚችል አስበው።
  • ምን ይፈጠራል?
  • ጅብ ሁለቱንም ይቀረጥፋል።
  • ሁለቱንም ማለት?
  • መጋቢውንም፣ የሥራ ዕድሉንም።
  • የጀመሩት ፕሮጀክቶች ፋይዳ አልገባሽም ብቻ ሳይሆን የሚገባሽ አይመስለኝም።
  • እንዴት አይገባኝም?
  • ቢገባሽማ እንዲህ ያሉ ማንም ሞክሯቸው የማያውቃቸውን ልዩ ሥራዎች አታጣጥይም ነበር።
  • ማንም ሞክሯቸው የማያውቃቸው ነው ያልከው?
  • አዎ!
  • እርግጥ ነው ጅብ የመመገብ ፕሮጀክት የቀረፀ መንግሥት በአገራችንም ሆነ በዓለም መንግሥታት ታሪክ ተሰምቶ አይታወቅም።
  • ፌዙን ተይውና እውነቱን ብትቀበይ ይሻላል።
  • የምርህን ነው?
  • አዎ።
  • እስኪ ንገረኝ፣ በማንም ተሞክሮ አያውቅም የምትለው የትኛውን ሥራ ነው?
  • ማዕድ ማጋራት!
  • እኔ ይህ የመንግሥት ሥራ አይመስለኝም። የመንግሥት ሥራ ሀብት መፍጠርና ሀብት ማከፋፈል መሆን አለበት ብዬ ነው የማምነው።
  • ማንም አይደፍረውም የምልሽ በዚህ ምክንያት እኮ ነው። አለ የምትይ ከሆነ ደግሞ ጥቀሺልኝ?
  • በእርግጥ ማዕድ ማጋራት በሌሎች ተቋማት እንጂ በመንግሥት የተለመደ ሥራ አይደለም።
  • በሌሎች ተቋማት ማለት?
  • በሃይማኖት ተቋማት!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

[ክቡር ሚኒስትሩ በመኖሪያ ቤታቸው ቁጭ ብለው ከባለቤታቸው ጋር እራት እየበሉ ሳለ የመሬት መንቀጥቀጥ ያሉበትን ሕንፃ አርገበገበው]

ይሄ ነገር አሳስቦኛል። የቱ? ንዝረቱ ነዋ? የምን ንዝረት? የመሬት መንቀጥቀጡ? እ... እሱን እንዴት? ከዚህ በላይ ጠንከር ብሎ ቢመጣ አዲስ አበባ ላይ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ይዘገንነኛል። ምን ይፈጠራል? አብዛኛው ነዋሪ ኮንዶሚኒየም ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ካምፕ የሚገቡ ታጣቂዎችን መልሶ የማቋቋምና ወደ ማኅበረሰቡ የመቀላቀል ኃላፊነት ከተሰጠው ኮሚሽን ኃላፊ ጋር እየተወያዩ ነው]

እሺ... ሥራው እንዴት እየሄደ ነው ኮሚሽነር? ክቡር ሚኒስትር... እስካሁን ያለው ሁኔታ መልካም ነው። መልካም ነው ማለት? ለሰሜኑ ክልል ቅድሚያ ሰጥተን ነው ሥራውን የጀመርነው። እና የተፈጠረ ችግር አለ? በጀመርንበት ክልል...