Saturday, September 30, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለክትትልና ግምገማ የተሰማሩት ከፍተኛ አመራሮች ያገኙትን ውጤት ሪፖርት ያደረጉበት የቴሌቪዥን ፕሮግራምን የሚኒስትሩ ባለቤት ለብቻቸው በመገረም እየተከታተሉ ሳለ ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ዘለቁ] 

  • እኔ ብቻ ይሆን ግን እንዲህ የምሆነው?
  • ምን ሆንሽ?
  • ግርም፣ ብግን የሚያረገኝ?
  • ምንድነው ያስገረመሽ?
  • የምትሠሩት ነገር ሁሉ ግርም ይለኛል።
  • እንዴት… ምን ሰምተሽ ነው?
  • ውይይቱ ላይ የሚባሉት ነገሮች ናቸው?
  • ምን ሲባል ሰምተሽ ነው?
  • ክልሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የመደመር ትውልድ መጽሐፍ በመሸጥ 360 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ቢያቅድም እስካሁን የሰበሰበው ግን 25 ሚሊዮን ብር ብቻ ነው ይላሉ።
  • እና…?
  • እናማ በቀሪዎቹ ሐምሌና ነሐሴ ወራት መጽሐፉን ለማኅበረሰቡ በስፋት በመሸጥ ያቀዱትን ገቢ እንዲሰበስቡ ከክልሉ አመራሮች ጋር ተግባብተናል ይላሉ።
  • ታዲያ ይኼን ማለታቸው ምን ያስገርማል?
  • የክልሉ ማኅበረሰብ አርሶ አደር መሆኑን አስቤ ነዋ?
  • አርሶ አደር ቢሆንስ?
  • የእርሻ ወቅት ሳያልፍ ማዳበሪያ ይቅረብልኝ ብሎ ሰላማዊ ሠልፍ ለወጣ አርሶ አደር ምን ሊቀርብለት እንደሆነ አስቤ ነዋ?
  • ምን ሊቀርብለት ነው?
  • የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ነዋ!
  • እያሾፍሽ ነው?
  • ኧረ በጭራሽ! ኧረ ሌላም ጉድ አለ። ሚኒስትሩ የሚሉትን ስማ …
  • ሰማሃቸው?
  • በቅጡ አልሰማሁም፣ ምን አሉ?
  • ሆሆ… መቼም ዘንድሮ ጉድ ነው የምሰማው።
  • ምንድነው ያሉት?
  • የሐረሪ ክልል የጠቅላይ ሚኒስትሩን የመደመር ትውልድ መጽሐፍ ሸጦ በሚያገኘው ገቢ የሚተገብረውን ፕሮጀክት እየገለጹ ነበር።
  • እኮ ምን አሉ? ፕሮጀክቱ ምንድነው?
  • የመደመር ትውልድ መጽሐፍን ሸጦ በሚያገኘው ገቢ የጅብ ምገባ ትርዒትን ያለማል ነው የሚሉት።
  • ታዲያ ምኑ ነው ያስገረመሽ?
  • የምታቅዱት ፕሮጀክቶች ናቸዋ!
  • እንዴት? ይኼ ምን ያስገርማል?
  • ማኅበረሰቡ የሚቀምሰው ተቸግሮ እያማረረና የኑሮ ውድነት ትርዒት እየሠራበት መሆኑ ጠፍቶህ ነው?
  • የኑሮ ውድነት ችግር መኖሩንማ መንግሥትም አልካደም።
  • እሱ እኮ ነው የሚገርመኝ?
  • ምኑ?
  • መንግሥት የማኅበረሰቡን መሠረታዊ ችግር እያወቀ የጅብ ምገባ ትርዒት ለማበልፀግ ፕሮጀክት መንደፉ።
  • ለአካባቢው ማኅበረሰብ የሥራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑ ጠፍቶሽ ነው?
  • እንዴት ሆኖ?
  • ለምን አይሆንም?
  • በጅብ ምገባ የሥራ ዕድል ለመፍጠር?
  • አዎ!
  • ቢፈጠር እንኳ የሥራ ዕድል ነው ለማለት ይቸግረኛል።
  • ለምን?
  • ጅብ የመመገብ የሥራ ዕድል መጨረሻው አያምርም።
  • ለምን?
  • መንግሥት በጀት አጠረኝ ብሎ ምግብ ማቅረቡን ያቋረጠ ቀን ምን ሊፈጠር እንደሚችል አስበው።
  • ምን ይፈጠራል?
  • ጅብ ሁለቱንም ይቀረጥፋል።
  • ሁለቱንም ማለት?
  • መጋቢውንም፣ የሥራ ዕድሉንም።
  • የጀመሩት ፕሮጀክቶች ፋይዳ አልገባሽም ብቻ ሳይሆን የሚገባሽ አይመስለኝም።
  • እንዴት አይገባኝም?
  • ቢገባሽማ እንዲህ ያሉ ማንም ሞክሯቸው የማያውቃቸውን ልዩ ሥራዎች አታጣጥይም ነበር።
  • ማንም ሞክሯቸው የማያውቃቸው ነው ያልከው?
  • አዎ!
  • እርግጥ ነው ጅብ የመመገብ ፕሮጀክት የቀረፀ መንግሥት በአገራችንም ሆነ በዓለም መንግሥታት ታሪክ ተሰምቶ አይታወቅም።
  • ፌዙን ተይውና እውነቱን ብትቀበይ ይሻላል።
  • የምርህን ነው?
  • አዎ።
  • እስኪ ንገረኝ፣ በማንም ተሞክሮ አያውቅም የምትለው የትኛውን ሥራ ነው?
  • ማዕድ ማጋራት!
  • እኔ ይህ የመንግሥት ሥራ አይመስለኝም። የመንግሥት ሥራ ሀብት መፍጠርና ሀብት ማከፋፈል መሆን አለበት ብዬ ነው የማምነው።
  • ማንም አይደፍረውም የምልሽ በዚህ ምክንያት እኮ ነው። አለ የምትይ ከሆነ ደግሞ ጥቀሺልኝ?
  • በእርግጥ ማዕድ ማጋራት በሌሎች ተቋማት እንጂ በመንግሥት የተለመደ ሥራ አይደለም።
  • በሌሎች ተቋማት ማለት?
  • በሃይማኖት ተቋማት!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...

ማን በማን ላይ ተስፋ ይኑረው?

በአንድነት ኃይሉ ችግሮቻችንን ለይተን ካወቅን መፍትሔውንና ተስፋ የምናደርግበትን ማወቅ እንችላለን፡፡...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ሳምንት ያክል የፓርቲ ስብሰባ ላይ ቆይተው አመሻሹ ላይ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ባለቤታቸው በአግራሞት ተቀብለው ስለቆይታቸው ይጠይቋቸው ጀመር]

እኔ እምልክ...? ውይ... ውይ... በመጀመሪያ እንኳን በሰላም መጣህ፡፡ እሺ ...ምን ልትጠይቂኝ ነበር? ይህን ያህል ጊዜ የቆያችሁት ለስብሰባ ነው? ስብሰባ ብቻ አይደለም። ከስብሰባ ውጪ ምን ነበር? በተለያዩ መሪ ሐሳቦች የተዘጋጁ ሥልጠናዎችን...

[ክቡር ሚኒስትሩ ለሁለት ቀናት የተካሄደውን የፓርቲያቸውን የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ አጠናቀው ወደ ቢሯቸው ሲመለሱ ቢሯቸው ውስጥ አማካሪያቸው አንድ ጽሑፍ በተመስጦ እያነበበ አገኙት]

ምንድነው እንደዚህ መስጦ የያዘህ ጉዳይ? መጡ እንዴ ክቡር ሚኒስትር፣ የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ያወጣውን መግለጫ እያነበብኩ ነው፡፡ ግን እኮ ፊትህ ላይ የመገረም ስሜት ይነበባል፡፡ አዎ፣ መግለጫው ላይ...

[ክቡር ሚኒስትሩ እየጠራ ያለውን ሞባይል ስልካቸውን ተመለከቱ፣ የህዳሴ ግድቡ ተደራዳሪ መሆናቸውን ሲያውቁ ስልኩን አነሱት]

ሃሎ... ጤና ይስልጥኝ ክቡር ሚኒስትር? ጤና ይስልጥልኝ ክቡር ተደራዳሪ... የጥረትዎን ፍሬ በማየትዎ እንኳን ደስ አለዎት፡፡ እንኳን አብሮ ደስ አለን፣ ምን ልታዘዝ ታዲያ? የውኃ ሙሌቱንና አጠቃላይ የግድቡን የግንባታ ሁኔታ...