አንዲት እናት ልጅዋ በእኩለ ሌሊት ነቅቶ እያለቀሰ ስላስቸገራት ‹‹ዝም በል አንተ ለቅሶህንም አላቆም ካልህ አውጥቼ ለጅብ ነው የምሰጥህ፡፡ ና ብላው አያ ጅቦ›› ስትል ልጁ ፈርቶ ዝም አለ፡፡ ነገር ግን ለካስ አንድ ጅብ በጓሮ በኩል ደፍጦ ሲያዳምጥ ካሁን አሁን አውጥተው ይጥሉታል ብሎ በመጠበቅ ላይ ነበርና በር ተንኳኳ፡፡ ‹‹ማነህ?›› ሲባል፣ ‹‹ኧረ የልጁ ጉዳይ ከምን ደረሰ?›› አለ ይባላል፡፡
- መክብብ አጥናው ‹‹ሁለገብ የአእምሮ ማዝናኛ›› (2005)