Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊፊንጫ አመርቲነሼ ኃይል ማመንጫ በብልሽት ምክንያት ሥራ አቆመ

ፊንጫ አመርቲነሼ ኃይል ማመንጫ በብልሽት ምክንያት ሥራ አቆመ

ቀን:

የፊንጫ አመርቲነሼ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በብልሽት ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቆመ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን በ237.8 ሚሊዮን ዶላር ያስገነባው የፊንጫ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ፣ 97 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም ነበረው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንጫ ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዳርጌ እሸቴ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የፊንጫ አመርቲነሼ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባጋጠመው የቴክኒክ ብልሽት በአሁኑ ወቅት ኃይል እያመነጨ አይደለም፡፡

‹‹ችግሩን በመፍታት ጣቢያው ኃይል እንዲያመነጭ ማድረግ የሚያስችሉ መሣሪያዎች ግዥ ተፈጽሞ ወደ አገር እየገቡ ነው፡፡ ዕቃዎቹን የሚያቀርበውም ቀደም ሲል ግንባታውን ያካሄደው ሲጂጂሲ ኦሲ ኩባንያ ነው፤›› ሲሉ አቶ አንዳርጌ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የፊንጫ አመርቲነሼ ፕሮጀክት ግንባታ ያካሄደው የቻይናው ሲጂጂሲ ኦሲ ኩባንያ  ሲሆን፣ ግንባታውን ካጠናቀቀ በኋላ ለተፈጠሩ ችግሮች ማረሚያዎችን አካሂዶ ፕሮጀክቱን እንዲያስረከብ ማሳሰቢያ እንደተሰጠው ሪፖርተር መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ኩባንያው ይህንን ሥራ አጠናቆ ካስረከበ በኋላ የገናሌ ዳዋ ቁጥር ሦስት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ተረክቦ ግንባታውን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

የቻይናው ኩባንያ ሲጂጂሲ ኦሲ ፕሮጀክቱን ካስረከበ በኋላ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቢሆንም፣ የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ያጋጠመውን ችግር ፈትቶ ወደ ሥርጭት ማስገባት አለመቻሉን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ፊንጫ በቴክኒክ በኩል ካጋጠመው ችግር በተጨማሪ ወደ ግድቡ የሚገባው ውኃ መጠንም አጥጋቢ እንዳልሆነ እየተገለጸ ነው፡፡

አቶ አንዳርጌ እንደሚሉት፣ እስካሁን ከተወሰኑ ግድቦች በስተቀር በአጠቃላይ በክረምቱ ወራት የጣለው ዝናብ በቂ ባለመሆኑ የውኃ አገባቡ አጥጋቢ አይለም፡፡

ነገር ግን አጠቃላይ ግድቦቹ የያዙት ውኃ የሚታወቀው በመስከረምና በጥቅምት ወራት ነው፡፡ በሚቀጥሉት ወራት የክረምቱ የዝናብ መጠን የተሻለ ይሆናል ተብሎ ስለሚጠበቅ፣ በተፈጠሩ የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት ግን በኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት በኩል ችግር እንዳልተፈጠረ አቶ አንዳርጌ ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥም ሆነ  የአቅርቦት ችግር እየተስተዋለ መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...